Tuesday, September 22, 2015

በኢትዮጵያ አየር መንገድ መስተንግዶ እንደ ሁለተኛ ዜጋ መታየታቸውን የሚገልጹ ኢትዮጵያውያን ደንበኞች ቅሬታ አሰሙ።


ከቅርብ ግዜ ወዲህ ወደ መካከለኛው ምስራቅ የሚጓዙ መንገደኞችን በአሮጌው ተርሚናል በኩል በማስተናገድ ላይ የሚገኘው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዜጎች በማንነታቸው ተለይተው እየተዋከቡ መሆኑን መንገደኞቹ የደረሰባቸውን በደል ዋቢ በማድረግ ምንጮች ይገልጻሉ በተለይ ወደ ሳውዲ አረቢያ የሚጓዘው ኢትዮጵያውያዊ አብዛኛው ሙስሊም ማህበረሰብ እንደመሆኑ መጠን ጥብቅ ቁጥጥር እና ክትትል እንደሚደረግባቸው የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች ዜጎች በገዛ ሃገራቸውና አየር መንገዳቸው እንደ ሁለተኛ ዜጋ መታየታችው የመንግስት እጅ እንዳለበት አመላካች መሆኑን ይጠቁማሉ። በአሮጌው ተርሚናል የሚስተናገድ እንዚህ የአየር መንገዱ ተገልገላይ ኢትዮጵያውያን ደንበኞች ኢዘውት በሚወጡትና በሚገቡት እቃዎቻቸው ላይ ያለአግባብ ጥብቅ ፍተሻ ይደረጋል ለቤተሰብ ዘመድ አዝማድ ስጦታ የሚውል እቃዎቻቸው ላይ ከፈተኛ ቀረጥ ይጣላል የመንገደኛው ሻንጣ ቁልፍ ተሰብሮ ይዘረፋል ሻንጣዎቹ እስክነ አካቴው የውሃ ሽታ ሆነው ይቀራሉ በዚህ ተርሚናል የሚስተናገዱ ደንበኞች በአየር መነግዱ ሰራተኞች ክብር አይሰጣቸውም መብቱን ለማስከበር ለምን ? ብሎ የጠየቀ መንገደኛ የሰደባል ይገለመጣል አልፎ አልፎ በጥፊና በካልቾ የሚሰተናገድበት አስዛኝ አጋጣሚ እንደሚከሰት የአይን እማኞች ገልፀዋል። ከሁሉም በላይ የሚያሳዝነው እና የከፋው ሳውዲ አረቢያ « መካ » ለሃጅ የፀሎት ሥረዓት በቤተሰብ አጀብ የሚሸኙ የጸሎት ተጓዥ ምእመናን ወደ አሮጌው ተርሚናል ከገቡ በሃላ እንደ ፀሎት ተጓዥ ሳይሆን አንደ አንድ መንገደኛ ማግኘት የሚገባቸውን ክብር አጥተው ስረዓት በሌላቸው አንዳንድ የአየር መንገዱ አስተናጋጆችና የፀጥታ አባላት እንደ ሚዋከቡ በደሉ የደረሰባቸውን ዜጎች ዋቢ በማድረግ ይገልጻሉ

ኢትዮጵያ አየር መንገድ በአሮጌው ተርሚናል እያደረገ ካለው የወረደ መስተንግዶ ይልቅ « ጅዳ » ሳውዲ አረቢያ አየር ማረፊያ በባዕዳኑ የአየር መንገዱ ሰራተኞችና የፀጥታ ሃይሎች የሚደረጉላቸው አቀባበልና / መስተንግዶ ምንም እንደ ማይገናኝና የትየለሌ መሆኑንን ሰሞኑን ጅዳ ከገቡ ምዕመናን የሃጅ ጸሎት ተጓዥ ሙስሊም ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን ማረጋገጥ ተችሏል። የኢትዮጵያ አየር መንገዱ መስተንግዶ መንግስት ሃገር ውስጥ በጋራ እና በተናጠል ህዝበ ሙስሊሙ ተቋም ላይ ከሚፈጽመው በደል አይለየም የሚሉ አንዳንድ ወገኖች በአሮጌው ተርሚናል በኩል የሚያልፍ ኢትዮጵያዊ ሙስሊም እንደ ዜጋ ቀርቶ አንድ ቆዳው ነጣ ያለ መንገደኛ የሚሰጠውን ክብር ያህል ቦታ የለንም ይላሉ። የኢትዮጵያ አየር መንገዱ መስተንግዶ በኢትዮጵያዊን ሙስሊም ወገኖቻችን ላይ ብቻ ያነጣጠር ይሁን እስካሁን ማረጋገጫ ለማግኘት ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም «ከተላብ የተገኘ ስሊጥ አብረህ ተወቀጥ » እንዲሉ በኮንተራት ስራም ሆነ በተለያዩ ምክንያቶች ወደ ተጠቀሱት ሃገርት የሚሄዱ ኢትዮጵያውያን ሳይቀሩ በደሉ እየተፈፀመባቸው መሆኑን የደረሰን መረጃ ያመለክታል። የሃገሪቱን ብሄራዊ ሰንደቅ ዓላማ አርማው በማድረግ ከግማሽ መዕተ አመት በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው ይህ ንብረትነቱ የኢትዮጵያ ህዝብ የሆነው አየር መንገድ በገዥው ፓርቲ .../.... ስረአት ካድሬዎች እጅ ከወደቀ ወዲህ ዜጎች በማንነታቸው እየተለዩ የዜግነት ክብራቸውን የሚያጡበት ብቻ ሳይሆን የአየር መንገዱ ሰራተኞች ጭምር በብሄር ማንነታቸውና በፖለቲካ አመለካከታቸው እየተለዩ ግፍና በደል የሚፈፀምባቸው ማዕከል እየሆነ መምጣቱ ይታወቃል። ህወሃት/.... ስረዓት የዜጎችን ከሃገር ወደ ሃገር የመዘዋወር ህገመንግስታዊ መበት በመጣስ ከሳውዲ አረቢያ ቤተዘመድ ጥየቃ ለረእፍት ወደ ኢትዮጵያ የሚጓዙ ዜጎች የዕረፍት ግዜያቸውን ጨርሰው ሲመለሱ የሚኖሩበትን ሃገር የመኖሪያ ፈቃድ መታወቂያ « ኢቃማ » ካላመጣችሁ አታልፉም በሚል ምክንያት በአየር መንግዱ ውስጥ በተሰገሰጉ የፀጥታ ሃይሎች እስከ 10 ሺህ ሪያል የሚደርስ ጉቦ በግልጽ እንደሚጠየቁ ለመረዳት ተችሏል። በሳውዲ አረቢያ ህግ ማንኛውም የወጭ ሃገር ዜጋ ፓስፖርቱን ከአሰሪው እጅ ሲቀበል የመኖሪያ ፈቃዱን ለኣሰሪው ማስረከብ እንደሚገባ ይደነግጋል። Ethiopian Hagere Jed Bewadi