Wednesday, July 30, 2014

«አሳዛኝ ዜና »ህክምና ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን በህይወት የመቆየት እድላቸው አስተማማኝ እንዳለሆነ የሆስፒታሉ ሚስጥራዊ ምንጮች ገለጹ

 ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ  ጅዳ ከተማ አንድ ሆስፒታል  «ቡግሻን» hospital ተኝተው  የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን የህክምና ግዜያቸውን  ሳይጨርሱ ከሆስፒታሉ እንዳይርቁ ዶክተሮቹ አስጠነቀቁ ፡፤  የመንግስት ባለስልጣኑ ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን ሲያቀኑ በሁለት እና በሶስት ቀናት የተጠቀሰውን ህክምና በአጭር ግዜ ውስጥ አጠናቀው  እንደሚመለሱ ተስፋ ቢያደርጉም ቀደም ብሎ ደቡብ አፍሪካ ላይ የተደረገላቸው የልብ  ህክምና ባለስልጣኑን ለከፋ አደጋ ሳይዳርጋቸው እንዳልቀረ የሚገልጹት የሆስፒታሉ የምርመራ ምንጮች  አቶ በረከት ስምኦን ዕረፍት ካልወሰዱ እና የዶክተሮች ቀርብ ክትትል ካልተደረገላቸው በህይወት ሊቆዩ እንደማይችሉ አስታውቀዋል።
አቶ በረከት በአሁኑ ሰአት በተጠቀሰው ሆስፒታል ውስጥ የእግር እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ዶክተሮች እንዳዘዟቸው እና የሆስፒታሉ አርማ ያረፈበት  የማታልብስ «ቢጃማ» መስል ነገር ለብሰው  4 ፎቅ ሲዊት ሩም 501 በረዳ ላይ ከአንድ ረዘም ካለ ደንዳን ሰውነት ካለው ሰው ጋር ሲጓራደዱ መታየታቸውን የአየን እማኞች አረጋግጠዋል። አቶ በረከትን ለማረጋጋት አላሙዲን በስልክ እና በአካል ከሚያደርጉላቸው ማጽናናት ውጭ እስካሁን ሄዶ ያያቸው ዲፕሎማተም ሆነ የመንግስት ባለስልጣን እንደሌለ እየተነገረ እንዚህ እማኞች ገልጸዋል። 
ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከትን አልፎ አልፎ ወሰድ « ፌንት »  የሚያደርጋቸው ነገር የልብ ምት አለመስተካከል መሆኑን በድፍረት መናገር ቢቻለም  የኚህን የመነግስት ባለ ስልጣን እድሜ መገመት አግባብ እንዳልሆነ የገለጹ አንድ ስለ አቶ በረከት ጤንነት በቀርብ የሚከታተሉ ዶክተር ለታካሚውም ሆነ ለቤተሰቦቹ ታካሚው ይሞታል  ብሎ መናገር ሙያዊ ስነምግባር እንዳልሆነ ተናግረው ታካሚው የልብ ምታቸው ተሰተካ ክሎ ከዚህ ሆስፒታል በሰላም መውጣት ከቻሉ ቀሪው የፈጣሪ ነው ብለዋል። እንደሚታወቀው እኚሁ ሚኒስቲር የዶክተሮችን የሰጧቸውን መረጃ አብነት በማድረግ   የቀድሞው የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር የጤነንት ጉዳይን አስመልከተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ጠቅላይ ሚንስትር መለሰ ዜናዊ   የጤንነታቸው ሁኔታ ተስተካክሎ በቀርብ ግዜ ወደ ነበሩበት መደበኛ ስራ እንደሚመለሱ ለኢትዮጵያ ህዝብ በገለጹ ማገስት ጠቅላይ ሚንስትሩ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው  የሚታወስ ነው ። Meles Zenawi is not dead, says Bereket Simon 
በአሁኑ ሰአት የመግስት ባለስልጣኑ መረጋጋት እንደማይታይባቸው እና አልፎ አልፎ እንደ  እንቀልፍ ቢጤ ጭልጥ አድርጎ የሚወስዳቸው ነገር ከልብ ምት አለመስተካከል ጋር የተያያዘ የሚፈጠር አደገኛ ነገር መሆኑን የተለያየ ሙያዊ ግምታቸውን  የሚሰጡ  የአካባቢው ታዛቢዎች በእንደዚህ አይነት መልኩ ወደ ሆስፒታሉ ለህክምና ከገቡ  ሃብታሞች እና ታዋቂ ሰዎች በሰላም ህይወታቸው ተርፎ  የወጡ ጥቂቶች ብቻ በመሆናቸው የአቶ በረከት ህይወተም ከጥቂቶቹ አንድ ይሆን ዘንድ እያለቀሱ  ሃዘናቸውን  ገልጸዋል። 
ይህ መረጃ እስከተጠናክረበት ግዜ ድረስ አቶ በረከት ስሞኦን በህይወት መኖራቸውን ያረጋገጡለን የአይን እማኞች የኢትዮጵያ መንግስት ሎኡካን ቡድን  ሰሞኑን ለጉብኘት በይፋ ወደ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ እንደሚመጣ እና የአቶ በረከት ስሞኦን የጤንነት ሁኔታ አስተማማኝ ካለሆነ መንግስት ቅድመ ዝግጅቶችን ማድረግ እንዲያስችለው ለኢትዮጵትያ ህዝብ በይፋ ሊገለጽ  እንደሚችል ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ያገኙትን ምስጢራዊ መረጃዎቻቸውን አድረስውናል ። Ethiopia - Information Minister, Bereket Simon Press conference on the death of Meles Zenawi 


ማሳሰቢያ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ስለኚህ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ ለመረዳት የሚፈልግ ወገን ለትክክለኛ መረጃ እንደ  አመቺነቱ የሆስፒታሉን ስልክ ቁጠር ከወዲሁ ለመግለጽ ይሞከል።                             ምንጭ ታምራት ይደጎ 

Sunday, July 27, 2014

ሰበር ዜና የአቶ በረከት ስምኦን የጤንነት ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን የሆስፒታል ምንጮች ገለጹ።

                    
 ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ ለህክምና የገቡት እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በተለምዶ   ብግሻን የሚባል አንድ ትልቅ ሆስፒታል  4 ፎቅ የልብ ቀዶ ጥገና በተሰካ ሁኔታ እንደተደረገላቸው የሚናገሩ ውስጥ፡ አውቂ ምንጮች ከቀዶ ጥገና ክፍሉ ከወጡ በሃላ የባለስልጣኑ የጤንነት ሁኔታ ወደ ነበረበት ሊመለስ ባለመቻሉ ወደሌላ ክፍል ተዘዋውረው የቀርብ ክትትል   እየተደረገላቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ይህ በንዲህ እንዳለ አቶ በረከት ስምኦን  ወደተኙበት ክፍል ዶክተሮች ባልተለመደ ሁኔታ እየተቻኳሉ ሲገቡ እና ሲወጡ ያዩ  የአይን እማኞች የባለስልጣኑንን በህይወት መትረፍ  ይጠራጠራሉ።
ከአንድ ቀን በፌት እዚህ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን ማካኝነት አንድ ኢትዮጵያዊ ዶክተር አስከትለው   ለህክምና እንደገቡ የሚነገረው አቶ በረከት ስምኦን እስካሁን ስላሉበት ሁኔታ በትክከል  መናገር ባይቻለም   አብረዋቸው ከመጡት የቀርብ ቤተሰቦቻቸው ውስጥ ሚስታቸው እና ሴት ልጃቸው ሆስፒታል ውስጥ ነጠላቸውን ወገባቸው ላይ አስረው ሲላቀሱ ያዩ ታዛቢዎች  የባለስልጣኑን  በህይወት መኖር ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደከተተው ይነገራል።  ለአቶ በረከት አርቴፊሻል የፕላስቲክ ቧንቧ ከልባቸውጋር በድጋፍ የተገጠመ መሆኑን የሚገልጹት የሆስፒታሉ ምንጮችየባለስልጣኑን የልብ መት የሚለካ ግስቲር በተጓዳኝ መገጠሙን  እና የልብ ቀዶ ጥገናው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን  ያረጋግጣሉ።
አቶ በረከት ስሞኦን ቀደም በልው ድቡብ አፍሪካ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ የልብ ቀዶ ጥገና ተደርጎላቸው እንደነበር የሚያሳዩ መረጃዎች ምናልባት በልብ ቀዶ ህክምናው ወቅት ስህተቶች ተፈጥረው በመንግስት ባላስልጣኑ ላይ አደገኛ ኢንፌክሸን ሳይፈጠር እናዳልቀር ይነገራል። አቶ በረከት ስሞን አሁን ስላሉበት የጤንነት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም ያለው ነገር ባይኖረም ስለእህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ ለመስብሰብ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት  የሚገኙ አንዳንድ ዲፕሎማቶችን ለማነጋገር ያደረኩት ሙከራ እስካሁን አልተሳካም ።   ምንጭ   ታምራት ይደጎ  

Wednesday, July 9, 2014

አንበሳውን በጅቦች ተከቦ አየሁት ( በፋሲል የኔአለም )


ኢቲቪ የአንዳርጋቸው ንግግር ነው ብሎ ያቀረበው ፊልም አስቂኝ ነው። እንደነ ቢቢሲ በኮርፖሬሽን ደረጃ ለመዋቀር በቃሁ የሚለው ድርጅት በሴኩርቲ ( በድብቅ )ካሜራ የተቀረጸ የደበዘዘና የተቆራረጠ ፊልም ሲያቀርብ ማፈር ነበረበት።
አንዳርጋቸው ከተያዘ 2 ሳምንታት አለፉ። ዛሬ በድብቅ ካሜራ ተቀርጾ የተላለፈው ፊልም በእለቱ ኢትዮጰያ ሲገባ የተቀረጸ ነው – አለማቀፍ ግፊት ቢበዛብን እናሳየዋለን ብለው ቀርጸው ያስቀመጡት ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ግን አንዳርጋቸው እያንዳንዷን ቀን በድብደባ እያሳለፈ ነው። ኢቲቪ ልብ ካለው አንዳርጋቸውን ላይቭ ያሳየን።
አንበሳው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚውል አንድም ነገር አልሰጣቸውም። “እኔ ስራየን ጨርሼ ደክሞኛል፣ እረፍት እፈለግ ነበር” ነው ያለው፤ ይህንን ደግሞ ዶ/ር ብርሃኑ ና ንቅናቄው አስቀድመው ተናግረውታል- አንዳርጋቸው ስራውን በጊዜ አጠናቆና ሃላፊነቱን ለወጣት አመራሮች ሰጥቶ እሱ መጠነኛ የዲፕሎማሲ ስራ እየሰራ ነበር።
ህወሃቶች በደንፎ “የትግራይን ህዝብ ትጠላለህ?” ብለው ጠየቁት። “ለማንም ህዝብ ጥላቻ የለኝም” ብሎ መለሰላቸው። አንዳርጋቸው የትግራይን ህዝብ ከጉጅሌው እንለየው የሚል ጽኑ አቋም ነበረው፣ያንን ነው የደገመው።
የታዩትን ፎቶግራፎች ድሮም አውቃቸዋለሁ፤ ከላፕቶፑ የተወሰዱ ናቸው። በእዚህ እድሜው የአውሮፓ ህይወቱን ትቶ በዛ አይነት ህይወት ለመኖር መፍቀዱ የሚደነቅ ነው። የእኔንም ኮምፒዩተር በቫየረስ በከሉት እንጅ እነዚህና ሌሎች ፎቶዎችም ነበሩኝ።
ፈገግታና ደግነት ደግሞ ባህሪው ነው። ጠላቶቹን ሳይቀር በፈገግታው ይገላቸዋል።
ከሁለት ሳምንት ድብደባ በሁዋላ ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ነገር አለማግኘታቸው ሃረር ውስጥ በጅቦች ተከቦ አልበላም ብሎ ሲታገል የነበረውን አንበሳ አስታወሰኝ።
ኮራሁብህ ወንድሜ አንዲ።

Tuesday, July 1, 2014

የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ ( ለኢህአዴግ ተላልፈው ከተሰጡ ድርጅቱ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ )

የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡
___________________________________________________
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም

የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።

ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።

መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።

በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።

በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

በርካታ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ንግድ ባንክ ከምዝገባ ውጪ ሊያደርገን ነው አሉ


ተጻፈ በ ታምሩ ጽጌ
‹‹በመቆጠቢያ ደብተራችን ትክክል የሆነው ስማችን በኮምፒውተር ስህተት ነው ተባለ››  ተመዝጋቢዎች
‹‹መቆጠቢያ ደብተር ላይ ብቻ ተመዝግቦ መገኘት ትክክል ነኝ አያስብልም›› የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በአዲስ አበባ ከተማ ከሁለት ዓመት በላይ የኖሩና ነባር ነዋሪዎች፣ የእነሱ ስህተት ባልሆነ ምክንያት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኮንዶሚኒየም ቤት ምዝገባ ውጪ ሊያደርጋቸው መሆኑን ተናገሩ፡፡
መመዝገብና መቆጠቢያ ደብተር ይዞ መገኘት የመመዝገቢያ መሥፈርትን ማሟላት እንዳልሆነ የሚገልጸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የሚያቀርቡት መረጃ ትክክል መሆኑ ከተረጋገጠና መረጃ ሲመዘገብ የተሳሳተ ከሆነ እንደሚስተካከል አስታውቋል፡፡
በተለይ የ20/80 አዲስ ተመዝጋቢዎች በየሚኖሩበት ክፍለ ከተማና ወረዳ በአግባቡ የምዝገባ መሥፈርቶችን ካሟሉ በኋላ የቁጠባ ደብተር መውሰዳቸውን ለሪፖርተር ገልጸው፣ አንዳንዶቹ የተወሰነ ጊዜ ከቆጠቡ በኋላና አንዳንዶቹ ደግሞ ገና ምንም ሳይቆጥቡ፣ በኮምፒውተር ላይ የተመዘገበው ስማችሁና በመቆጠቢያ ደብተሩ ላይ ያለው ስም ሙሉ በሙሉ አይመሳሰልም፡፡ የተወሰኑት ደግሞ ከራሳቸው፣ ከአባታቸው ወይም ከአያታቸው ስም ላይ አንድና ሁለት ፊደላት መጉደሉ እየተነገራቸው ‹‹መቆጠብ አትችሉም›› መባላቸውን አሳውቀዋል፡፡ 
ተመዝጋቢዎቹ በተለይ የተወሰነ ጊዜ ሲቆጥቡ የከረሙት ‹‹ይኼንን ያህል ጊዜ ከቆጠብኩ በኋላ ለምን እንደዚህ ያለ ጥያቄ ታነሳላችሁ? መጀመሪያውኑ ለምን አልነገራችሁንም?›› የሚል ጥያቄ ሲያነሱ፣ ምንም ምላሽ የሚሰጣቸው ማጣታቸውን የሚገልጹት ተመዝጋቢዎቹ፣ መጀመሪያ ወደተመዘገቡበት ቀበሌ በመሄድ ከባህር መዝገብ ጀምሮ በሙሉ የሞሏቸውን ቅጾች ሲመለከቱ ሁሉም ትክክል መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ 
ትክክለኛ ማስረጃ በመያዝ ወደ ባንክ ባለሙያዎቹ ሲቀርቡ ‹‹ችግሩ የአንድና የሁለት ሰው ሳይሆን የበርካቶች ስለሆነ፣ ጉዳዩ ለባንኩ ፕሬዚዳንት ተነግሯቸው ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ በመሆኑ ተረጋግታችሁ ጠብቁ፤›› የሚል ምላሽ እንደተነገራቸው አክለዋል፡፡
መንግሥት የመጀመሪያውን የኮንዶሚኒየም ምዝገባ ባካሄደበት ወቀት አጥተውት ሲቆጩ ከርመው ያገኙትን የምዝገባ ዕድል፣ በእነሱ ስህተት ሳይሆን በባንኩ ሠራተኞች ስህተት እንዳያጡት ሥጋት እንዳደረባቸው የሚናገሩት ተመዝጋቢዎቹ፣ የሚመለከተው አካል ጉዳዩን ተከታትሎ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ 
ተመዝጋቢዎቹ የሚያነሱትን ሥጋትና ተሳስቷል ስለሚሉት የምዝገባ ሁኔታ ለሪፖርተር ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሙኒዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ መመዝገብና መቆጠቢያ ደብተር ይዞ መገኘት የመመዝገቢያ መሥፈርትን ማሟላት አይደለም፡፡ ቢያንስ በመንግሥት እንዲቆጠብ የተነገረውን የመጨረሻውን የቁጠባ ሒሳብ መቆጠብ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፣ ተመዝጋቢዎች ለመመዝገብ የሚያበቋቸውን መሥፈርቶች አሟልተው ስህተት የተፈጠረባቸው በባንኩ ከሆነ ተጣርቶ እንደሚስተካከል ተናግረዋል፡፡
ለምዝገባ ፕሮግራሞቹ በተሰጠው ቀነ ገደብ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተመዝጋቢዎች መመዝገባቸውን የገለጹት አቶ ኤፍሬም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመመዝገባቸው አንፃር ከ99 በመቶ በላይ በአግባቡ የተመዘገቡ መሆናቸውንና የተለያዩ ችግሮች አጋጥመዋል ቢባልም እጅግ በጣም ትንሽ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ለባንኩ የተለያዩ ችግሮች መቅረባቸውን ያልካዱት ሥራ አስኪያጁ፣ ተመዝጋቢዎቹ ከተመዘገቡ በኋላ ስማቸውን በፍርድ ቤት አስቀይረው በመምጣት እንዲስተካከልላቸው የሚጠይቁ አካሄዳቸው ሕጋዊ ቢሆንም፣ በባንኩ ላይ ጫና ማሳደሩ እንዳልቀረ ተናግረዋል፡፡ መቆጠቢያ ደብተር የሚጥሉና አካውንት ቁጥራቸውን የማያውቁ እንዳሉ፣ በአስተዳደሩ በኩል ሁሉንም ቅጾች በአግባቡ ከሞሉ በኋላ በመቆጠቢያ ደብተራቸው ላይ የማይመሳሰል ስም አስመዝግበው የሚቀርቡ መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ ሌላው የተመዝጋቢዎች ስህተት በውክልና ያስመዘገቡትን ሰው ስም ይተውና በመቆጠቢያ ደብተሩ ላይ የራሳቸውን ስም አስመዝግበው የሚቀርቡ እንዳሉ፣ የራሳቸው ስም ትክክል ከሆነ የአባት ወይም አያት ስም ሙሉ በሙሉ ስህተት ሆኖ የተመዘገቡ እንደሚያጋጥሙና በመጨረሻ ተመዝጋቢዎቹ የተናገሩት ከአባታቸው ወይም ከአያታቸው ስም ውስጥ ሁለት ወይም አንድ ፊደል ጎድሎ መመዝገቡ፣ በባንክ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ መሆኑን አቶ ኤፍሬም ገልጸዋል፡፡ 
ከ1,393 በላይ ተመዝጋቢዎች ስም ተጣርቶ ማስተካከያ እንደተደረገ የገለጹት አቶ ኤፍሬም፣ በቀጣይም ሌሎች አቤቱታ የቀረበባቸውን ለማስተካከል በማዕከል ደረጃ እየታየ መሆኑንና ትክክለኛ ሆኖ ከተገኘ የሚስተካከል መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተመዝግበውና መቆጠቢያ ደብተር ብቻ ይዘው ሳይቆጥቡ ዝም ብለው የከረሙ ካሉ፣ መሥፈርቱን አሟልተው ከተመዘገቡትና በወቅቱ የተወሰነውን መቆጠብ ከጀመሩት ጋር እኩል ስለማይታይ እንዳልተመዘገቡ እንደሚቆጠርም አቶ ኤፍሬም አክለዋል፡፡