Wednesday, August 27, 2014

የተማሪዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል (ሥርዓቱን ለ 20ዓመት አይተነዋል መቀየር አለበት!)


የተማሪዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል
(ሥርዓቱን ለ 20ዓመት አይተነዋል መቀየር አለበት!)
http://www.goolgule.com/university-students-protest-continues-ethiopia/

    የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው
    የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም
    የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል
    የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም

አዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ የአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ስልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡

የኢኮኖሚ እድገት

ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም “በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም” በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ “ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም” ማለታቸው ተገልጾአል፡፡

በተመሳሳይም “2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ “አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም” የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡

እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ “እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም “ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?” ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡

የባህር በር

ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እንዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል “በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው” በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡

የትምህርት ጥራት

ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ “ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም” በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም “የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም” በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡

ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ” ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

(ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ – ፎቶ ከፋይል ማህደር)


የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው

የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም

የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል
የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም
አዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ የአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ስልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡
የኢኮኖሚ እድገት
ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም “በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም” በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ “ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም” ማለታቸው ተገልጾአል፡፡
በተመሳሳይም “2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ “አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም” የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡
እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ “እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም “ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?” ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡
የባህር በር
ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እንዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል “በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው” በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡
የትምህርት ጥራት
ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ “ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም” በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም “የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም” በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡
ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ” ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
(ምንጭ: golgul  ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ – ፎቶ ከፋይል ማህደር)

ያልተገራው ገሪ …. ኢቲቪ (ጌታቸው ሺፈራው)


 
 
  •  
    Share
በጌታቸው ሺፈራው
ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ አገራት ነጻነታቸውን አግኝተው የዓለም ቀጣይ ኃያል አገራትን ተቀላቅለዋል፡፡ አብዛኛው የዓለም ማህበረሰብ ዴሞክራሲያዊ በሆኑ ስርዓቶች ለመተዳደር እድል አግኝቷል፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ግን ስልጣን ከያዘ ማግስት በህግ ፈቀድኩት ያለውን የሚዲያ ነጻነትን ጨምሮ በማፈን፣ በዛው በርሃ ውስጥ በነበረው ‹‹ውርጋጥነቱ›› ቀጥሏል፡፡ አሁንም ቢሆን ‹‹ሲቪል›› ነኝ ብሎ የሚያስበው በአፈሙዝ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዴሞክራትነቱን እያስወራ በተግባር ግን የአምባገነኖች ቁንጮ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በአጠቃላይ በርሃ ከነበረበትም በባሰ አሁንም እንዳፈተተው በኢትዮጵያውያን ላይ ስልጣኑን የሚያስጠብቅለትን እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል፡፡ ኢህአዴግ አልተገራም፡፡
safe_image
እንዲያም ሆኖ ግን ሌሎቹን ስለ መግራት ያወራል፡፡ ትናንትና ማታ (ነሐሴ 19/2006) በልሳኑ ያሳየው ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› የተሰኘ ፊልም የሚያሳየውም ይህንን ከአለ-አቅም መንጠራራትን ነው፡፡ ኃይሌና ገና በጋዜጠኝነት ተመረቁ የተባሉ ወጣቶች የእነ ፕሮፌሰር መስፍንን፣ የእነ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራን፣ የእነ ተመስገን ደሳለኝን፣ የእነ ዓለማየሁ ገላጋይን ብዕር ‹‹ሊገሩ›› ሲፍጨረጨሩ ማየት በእጅጉ የሚያስገርም ነው፡፡

ሲያሸንፍም በስሜት የዘለልንለት፣ ሲሸነፍ የተሸነፍንለት የድሮው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ከስርዓቱ ጋር አብሮ ‹‹ሚዲያ ኑክሊየር ነው!›› ሲል ‹‹አጥፊነቱን›› መስክሯል፡፡ በእርግጥ ኃይሌ በህዝብ ላይ ሲቀልድ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከአመት በፊት በሰይፉ ፋንታሁን የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ስለ መምህራን የደሞዝ ጭማሬ ተጠይቆ የመምህራኖቹ የደምወዝ ጭማሬ ቅብጠት መሆኑን ተናግሯል፡፡ ከአንድ አስተማማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳገኘሁት ከሆነ ኃይሌ ገብረስላሴ ለስርዓቱ አፋኝነትም በግልጽ ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ ነው፡፡ የመረጃ ምንጩ እንደጠቀሰልኝ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የሚታጎሩበት የካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማስፋፊያ የተሰራው በኃይሌ ገብረስላሴ የገንዘብ እገዛ ነው፡፡ ለዚህ ፖሊስ ጣቢያ ካቴና ከውጭ አገር ያስመጣውም ኃይሌ ገብረስላሴ እንደሆነ ምንጩ ገልጾልኛል፡፡
በርካታ ኢንቨስትመንቶቹ በገዥው ፓርቲ ይሁንታ እንደሚቀጥሉ ያመነ የመሰለው ኃይሌ ትናንትናውም ቢሆን የስርዓቱ መሳሪያ ሆኖ ሚዲያውን ሲተች ያመሸው ከራሱ የኢኮኖሚ ጥቅም አንጻር ነው፡፡ ኃይሌ ከኑክሊየርም በላይ አፍራሽ ነው ያለውን ሚዲያ መተቸት የጀመረው በአንድ ዘገባ ምክንያት አንድ የውሃ ፋብሪካ መዘጋቱን በመግለጽ ነው፡፡ ኃይሌ ይህን ወደ ራሱ አስጠግቶ ሲያጠናክርም ‹‹በእኔ ላይ በመጻፉ ልጆቼ፣ ቤተሰቤ ያያሉ፡፡ በስሬ 1500 ሰራተኛ አለ፡፡ አዋሳ፣ ባህርዳር፣…ያሉት ሰራተኞችም ያዩታል፡፡ ሰራተኞችም ይህ ሰው ምን ነካው ይላሉ፡፡ ቢዝነስ ‹ኮላፕስ› ያደርጋል፡፡›› ሲል ነበር የገለጸው፡፡ እንግዲህ ገና የኃይሌ ልጅ ትሰማለች ተብሎ፣ ሰራተኞቹ ‹‹ምን ነካው!›› ስለሚሉ፣ ‹‹ቢዝነሱ ኮላፕስ›› ስለሚያደርግ ኃይሌ ምንም ያህል ቢያጠፋ ሚዲያው ትንፍሽ ላይል ነው ማለት ነው፡፡ ይህን የኃይሌን ሀሳብ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ውስጥ መምህር ነች የተባለችውም ‹‹የሰዎች ጓዳ (መቼስ ሚስጥር ማለቷ ነው) ሚዲያ ላይ መውጣት የለበትም፡፡›› ስትል ሀሳባቸውን ተሰብስበው የተስማሙበት አስመስላዋለች፡፡ በቃ ሚዲያ ሚስጥር የማውጣት ሚናውን በእነ ኃይሌ ዳኝነት ተቀማ ማለት ነው፡፡ እነ ኃይሌና ዶክተር አሸብር ለስርዓቱ ክንድ በሆኑበት በዛው ፊልም ላይ ካሳ ተከፍሏቸዋል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ኃይሌ ገብረስላሴ ሊወዳደር ነው፣ ዶ/ር አሸብር አምባገነን ነው›› የሚሉ ዜናዎችና ትችቶች ሳይቀር በአጥፊነት የተፈረጁላቸው፡፡
ሚዲያ ከሌለው መንግስት ይልቅ መንግስት የሌለው ሚዲያ ይሻላል የሚል መርህ የሚከተሉትን የእንግሊዝና የአሜሪካን ዴሞክራሲ አውቀዋለሁ ያለው ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሚዲያ ‹‹ያልተገራ›› በመሆኑ በሚያሳስብ መልኩ ያ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰለትን ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ራዕይ›› እናስጠብቃለን የሚሉ አካላት እርምጃ እንዲወስዱ ፍርደ-ገምድልነቱን አሳይቷል፡፡
ስርዓቱን የማዳን እርብርብ
በዚህ ፊልም ላይ ስለ ሰራዊት ፍቅሬ የፍቅር ደብዳቤ መጻፍ፣ በሞቅታ ስለሚጨፍሩት አርቲስቶች አስተያየት መስጠት በአውዳሚነት አስፈርጇል፡፡ ይህ የሆነው እነዚህ ‹‹ልማታዊ አርቲስቶች›› ያልተገራው ስርዓቱ ቅቡልነት እንዲያገኝ ሳይታክቱ የሚሰሩ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ‹‹አባይ ለፕሮፖጋንዳ አይዋል›› ማለት ብሄራዊ ደህንነትን ተጻርሮ የቆመ አስመስሏል፡፡ ከምንም በላይ ስርዓቱ ለስልጣኑ መሰረት አድርጎ የሚወስዳቸው አንጓዎች በሚዲያው ሊነኩ የማይገባ ‹‹ቀይ መስመሮች›› ተደርገው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ መቼም አንድ ተቃዋሚ መንግስትን የተቆጣጠረውን ፓርቲ ከስልጣን አውርዶ መንግስት ለመሆነ ነው የሚሰራው፡፡ ያልተገራው ‹‹መንግስት›› መሳሪያ የሆኑትና እነሱም ከስርዓቱ ጋር በጥቅም ከመጋራታቸው ውጭ የተገራ ነገር ያልታየባቸው ነገር ግን የተገሩትን ሲያጣምሙ የታዩት የፊልሙ ሰሪዎች ግን ‹‹ህዝብ ሌላ መንግስት ለማየት ፍላጎት አለው›› የሚለውን ከኑክሊየርም በላይ አጥፊ ነው ብለው ፈርጀውታል፡፡ ጋዜጠኝነት ‹‹በራዲካል ሮል›› ፖሊሲ የማስቀየር ሚና አለው ብለው ሳይጨርሱ ‹‹የብሄር ፌደራሊዝሙ እርምት ያስፈልገዋል›› የሚልን መካሪ ጽሁፍ በአሉታዊነት ለፈውታል፡፡ የ‹‹ብሄር ፖለቲካው›› ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም አይነት ያልተገራ አቋማቸውን ዳግመኛ አሳይተውበታል፡፡ ጠባብ አለመሆናቸውን ማሳመን ሲያቅታቸው ጠባብነታቸውን የሚተቹትን ሚዲያዎች ያልተገሩ ሲሉ ወርፈዋቸዋል፡፡ እነሱ አንዳንድ ተቋማት ስለ ‹‹መንግስት›› ያወጧቸውን መልካም የሚባሉ ነገሮች አመት ሙሉ እንደማይደጋግሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ስለ ድህነት፣ የመፈንቅለ መንግስት ስጋትና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያወጧቸውን ሪፖርቶች የግል ሚዲያው እንዳያወጣ ቅድመ ክልከላ አውጀዋል፡፡ ማጎሪያ ቤት ውስጥ ያለውን ስቃይ ማስተባበል ሲያቅታቸው ‹‹ማረሚያ የሚያስፈልገው ማረሚያ ቤት›› የተሰኘን መካሪ ጽሁፍ በህገ ወጥነት ፈርጀውታል፡፡
ኢህአዴግ የውድቀት ዋዜማ፣ ኢትዮጵያ ለምን አሚሶንን ተቀላቀለች? ፍትህ በሌለበት የፍትህ ሳምንት፣ ለአክራሪነት አስተማሪው ማን ነው? ለተሰኙት መልስ መስጠት ሲያቅታቸው፣ እውነት ሆኖ እንቅልፍ ሲነሳቸው በጸረ ሽብር ህጉ አውድ አሸባሪ ብለው ፈርጀዋቸዋል፡፡ በጣም የሚገርመው አብዛኛዎቹ ጽሁፎች በጥያቄ የቀረቡና ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርጉ ሲሆኑ ኢህአዴግ ግን ቀድሞ ‹‹እኔን ነው›› ብሎ ለራሱ ወስዷቸዋል፡፡ ሚዲያው ገለልተኝነቱን እያሳየም ቢሆን እነሱ የአንድ አካል አፈ ቀላጤ ይሉታል፡፡ ለዚህ እንደ ማስረጃ ያቀረቡት ደግሞ ‹‹ማንን እንመን?›› በሚል የወጣን አንድ ጽሁፍ ነው፡፡ ይህ ጽሁፍ ዶ/ር ብርሃኑንና በረከት ስምዖንን ያፋጠጠ ጽሁፍ ነው፡፡ ከሁለቱ አካላት ማንንን እንመን ተብሎ በማነጻጸሪያነት የወጣውን ይህን ጽሁፍ ራሱን የማያምነው ኢህአዴግ ‹‹እኔን ነው የማያምኑኝ›› ብሎ ጥፋቱን ቀድሞ ወስዶ ‹‹የአንድ አካል አፈቀላጤ ሆነዋል›› ሲል ይከሳል፡፡
በአጠቃላይ ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› በሚል የቀረበው ፊልም የኢህአዴግን ፖሊሲ መተቸት ህገ ወጥነት እንደሆነ የታየበት፣ የስርዓቱ ዋና ዋና የስልጣን ማቆያ ፖሊሲዎችን መንካት ስርዓቱን ሊያፈራርሰው እንደሚችል ባልተገራ አንደበት የተነገረበት ፊልም ነው፡፡ በፊልሙ ተዋናይ የሆኑት አካላት እዛው ፊልሙ ላይ ‹‹ፌቨር›› እየተሰራላቸው በትውልዱ ላይ ሲፈርዱ ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ እንደሆኑ በግልጽ ለማየት ተችሏል፡፡ ሁሉንም ነገር ከኢኮኖሚ አንጻር ሲቃኝ ያመሸው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦርነት ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኃይል በእጁ ለሆነው ያልተገራ ስርዓት በቅኔ እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል፡፡ የስፖርት ጋዜጦች ድረስ ተሂዶ የተደረጉበት ጥቃቅን ትችቶች በህገ ወጥነት የተፈረጁለት ዶክተር አሸብር በግልጽ አገልጋይነቱንና ስርዓቱን ለማዳን የቆመ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ፓርላማ ላይ ኢትዮጵያ ምንም አይነት ጥቅም ሳታገኝ ለጅቡቲ ውሃ የሚለግሰውን አዋጅ ከተቃወሙት መካከል ዶክተሩ አንዱ እንደነበሩ በሚዲያ ተገልጾ የነበር ቢሆንም ዶክተሩ ግን ስለ አዋጁ ያላቸውን ይሁንታ ሲገልጹ ‹‹ከእኛ ጋር ሳይደርስ ለምን አይጸድቅም?›› የሚል ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የህዝብ ተወካይ ነኝ ብሎ አንድን ህግ ‹‹ፓርላማ ሳይመጣ ለምን ራሱ ኢህአዴግ አያጸድቀውም›› ማለት ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
በአጠቃላይ በፊልሙ ላይ በአሉታዊነት የተፈረጁት ጽሁፎች ቢበዛ መካሪ ቢሆኑ እንጂ ይህ ነው የሚባል ‹‹አለመገራት›› አይታይባቸውም፡፡ ነገር ግን ባለመገራቱ ሳይነካ የሚደነብረውን ስርዓት ይበልጡን የሚያስበረግጉ መሆናቸው የሚያስገርም አይሆንም፡፡
እነ ኃይሌ ዴሞክራሲን አይቼባቸዋለሁ ባሏቸው አገራት ሚዲያ አራተኛ የመንግስት አካል ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስቱ የመንግስት አካላትም ሆነ መንግስት ባለመኖሩ አራተኛ መንግስት ሊሆን አልቻለም፡፡ ከዚህ ይልቅ መንግስት በሌለበት፣ ካልተገራ ዘመናዊ የቤተ መንግስት ወንበዴ ጋር ግብ ግብ የሚገጥም ብቸኛው የመንግስት አካል ሆኖ ለማገልገል ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ደግሞ መንግስትም ሆነ የመንግስት አካላት እንዳይኖሩ የሚፈልገውንና ልጥ ሲያይ እባብ ነው ብሎ የሚደነብር ያልተገራ ስርዓት እጅጉን አስደንብሮታል፡፡ ስለ ተገራና ስላልተገራ ብዕር ይህ ነው የሚባል እውቀት የሌላቸው፣ የማያገባቸው እነ ኃይሌም ያልተገራው ስርዓት ጋር የተጋሩትን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሉ ስርዓቱ በሚዲያው ላይ እርግጫውን በመሰንዘር እራሱን እንዲያድን እርብርብ አድርገዋል፡፡ የእነ ኃይሌ ምክር ስርዓቱ እንደለመደው እንዲራገጥ የሚገፋፋ ቢሆንም ማዳን አለማዳኑንም ሆነ እነሱ በትውልዱ ላይ እየፈጸሙት ያለውን በደል ግን ታሪክ የሚፈርደው ይሆናል፡፡

Tuesday, August 19, 2014

ሻእቢያ ከከረን እና ከአስመራ ጦሩን ወደ ተሰንይ ማስፈሩን ተከትሎ ወያኔ ተጨማሪ ጦር ሲያጓጉዝ ዋለ።

የመከላከያ ሰራዊቱ ሊከዳ ይችላል በሚል ስጋት የወያኔ ጄኔራሎች ሲመክሩ ውለዋል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ከሩሲያ ጋር የጦር ልምምድ ስምምነት እንዳደረገ የሚነገርለት የኤርትራ ገዥ ቡድን ሻእቢያ ከባለፉት ወራቶች ጀምሮ ጦሩን ወደ ደቡባዊ የኤርትራ ግዛቶቹ በመሰብሰብ ላይ መሆኑን ተከትሎ ወያኔም እንዲሁ ባለፈው ካሰፈረው ሰራዊት በተጨማሪ ከትላንትና ጀምሮ ከባድ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ተጨማሪ የጦር ሰራዊት በአከባቢው በማስፈር ላይ መሆኑ ታውቋል።

አሜሪካ እና ሩሲያ በአከባቢው ያላቸውን የበላይነት ለመቀዳጀት ፉክክር በገቡበት በዚህ ወቅት አከባቢው የጦርነት ቀጠና እንደሚሆን ቀድማ አሜሪካ በበረራ ደህንንነ ሰበብ ሹክ ባለችበት ሰአት እንዲሁም የሻእቢያ ተቃዋሚ ሃይሎችን ወያኔ በገንዘብ እና በቅስቁስ እየረዳ ባለበት ጊዜ በተጨማሪም በአግል ወያኔያዊ ትእቢት እየዛተ እንዳለ ሲሆን ለወያኔ ከፍተኛ ስጋት የሆኑበት ኢርታራ ውስት የመሸጉ ተቃዋሚ ሃይላት ስለሆኑበት በጭቆና የተምረረው ምከልከያ ሰራዊት ተቃዋሚዎችን ይቀላቅላል የሚል ከባድ ስጋት በሕወሓት ጄኔራሎች ላይ መከሰቱን ምንጮች ጠቁመውል።

ወያኔ በቅርቡ ከዩክሬይን ያስገባችቸን ቲ-72 ዘመናዊ ታንኮች በጦርነት ላይ ለማሰለፍ ወደ ሰሜን እያጓጓዘ ሲሆን ሻእቢያ በበኩሉ ሩሲያ ሰራሽ የሆኑ ዘመናዊ ታንኮች ሚሳኤሎች እና ከባባድ መሳሪያዎች፡ጸረ አይሮፕላን መድፎችን በአከባቢው አስፍሯል። ወያኔ ዘመናዊ መሳሪያ እና በታንክ ላይ የተጠመዱ መድፎችን ቢያምጣም በመክላከያ ሰራዊቱ ላይ ምንም አይነት መተማመን እንዳሌለው እየተናገረ ሲሆን በሰሜናዊ ትግራይ ብግብርና ሙያ ላይ ከነሙሉ ትጥቃቸው ያሰፈራቸውን የቀድሞ ታጋዮች እየቀሰቀሰ መሆኑ ሲታወቅ ህዝቡ ጦርነት እንደተሰላቸ እና ባለው ስርአት ላይ እምነት እንዳጣ በግልጽ እየተናገረ መሆኑ ታውቋል።

በሰራዊቱ ያልተማመነው ወያኔ አንድ የወሰደው እርምጃ ከሱዳን ጋር ያደረገውን የሰራዊት ቅልቅል ሲሆን ይህም ተቀላቅሎ መስራት በሰራዊቱ መኮንኖች ዘንድ ተቀባይነት አለማግኘቱ ታውቋል። የምዕራብ ኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ያሰበውን አገር የማጥፋት ሴራ ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን እና ሰራዊቱም ይህንን ተረድቶ ላገሩ ክብርና ታሪክ እንዲቆም ህዝቡ እየትናግረ ሲሆን የተደረገው የሰራዊት ውህደት ሱዳን በዳርፍርና ምስራቅ ሱዳን እንዲሁም ከደቡብ ሱዳን አቅጣጫ ላለበት ጦርነት በስምምነታቸው መሰረት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲዋጉለት ለማድረግና ወያኔም በዚህ ጉዳይ ላይ መስማማቱን እናም በመከላከያ ሰራዊት ያለ የኢትዮጵያ ወጣት በጎረቤት አገሮች የበረሃ ሲሳይ ከመሆን ራስን እንዲታደግ አስተያየት ሰጪዎች አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአዲስ አበባ የሚወጡ ዘገባዎች መጭውን የወያኔ የጦርነት ዝግጅት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ በመክዳት ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ሊቀላቀል ይሽላል በሚል ስጋት ስብሰባ ተቀምጠው መዋላችውን ምንጮች ጠቁመዋል። በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ሃይሎች የሚያወጡት መግለጫ በሰራዊቱ ላይ የሚፈጸመው ዘረኝነት እንዲሁም ብዝበዛ እና ከሃገሪቱ ጥቅሞች አንጻር እየተደረገ ያለው ብሄራዊ ውርድት በእጅጉ አሳሳቢ ደረጅ ልይ መድረሱ ሕዝቡ ለስር አቱ ያለው ጥላቻ መበራከቱ እንዲሁም ከዚህ ቀደም በባድመ ጉዳይ የተፈጸሙ መንግስታዊ ማጭበርበሮች እና የመሳሰሉት ግኡዳዮች ሰራዊቱ ይከዳል የሚል ከባድ ስጋት ያላቸው መሆኑን ያወሱት ጄኔራሎቹ በመከላከያ ሰራዊቱ ላይ እምነት በማጣትቸው ትግራይ ያለው የሕወሓት ታጣቂ ሃይል ከጀርባ እንደ ደጀን እንደ መተማመኛ እንደሚወስዱት መክረዋል።

ሰራዊቱ ያለውን ስርአት በተመለከት ደስተኛ ስላልሆነ እንዲሁም ሕዝቡ የሚፈልገው ለውጥ እንጂ ጦርንት ስላልሆነ ወያኔ በመጭው ሊያደርገው ያሰበው ጦርነት ከባድ ኪሳራ ያስክትልበታል ተብሎ ተገም

ለራሱ ነፃነት የሌለው ድረጀት የህዝቦችን ሰበአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መበት ተግባርዊ አያደርግም ! የመኢአድ ሰሞነኛ ውዝግቡ !

 መኢአድ በመጣባቸው አስቸጋሪ የትግል ጊዜያት አሁን ላይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ታህሣስ 15- 17, 2003 ዓ. ም ወዲህ በአመራሩ ላይ በደረሰ ክፍፍል ፓርቲው ይህ ነው የሚባል ስራ ለመስራት እየተውተለተለ እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2006 ዓ. ም ደርሶ በመካከሉ ይፈታል የተባለው የእርቅ ሂደት መና ሊቀር ችሏል፡፡

ጉዳዩ በፍ/ ቤትና በምርጫ ቦርድ ተይዞ መጠራቅቅ ውስጥ የወደቀው የፓርቲው ሕልውና የውስጥ ችግሩን ፈትቶ ከአንድነትና ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ተዋህዶ አንድ ወጥ ሀገራዊ  ችግር ይፈታል ተብሎ ሲታሰብ ‹‹ሽማግሌ›› ተብለው በተመረጡት በነ ዶ/ር በዛብህ ዝርክርክነት ያለውጤት በቁርሾ እንዲበተን ተደርጓል፡፡

ለአለመግባባቱ ምክንያት አቶ አበባው መሀሪ፣ ወያኔ አስርጎ ካስገባቸው፡- ሙላጌታ አበበ÷ ተስፋሁን አለሙ÷ መላኩ…እና ከትግራይ በወያኔ ተልከው ከመጡ መሰሉና ጋዳፊ በተባሉ‹ባልና ሚስት›(እነዚህ ቀደም ሲል በመኢአድ ውስጥ የትግራይ ተወካይ ነን በማለት መኖሪያ ቤታቸውን ቢሮ ነው በሚል ኪራይ ሲቀበሉና በጀት ተመድቦላቸው ሲያምታቱ የነበረ÷ ከ2004 ዓ. ም በኋላ አንድነት ፓርቲ ገብተው 4.000.00ብር በመቀበል አንዷለም አራጌን በመሰለል ለእስር ከአበቁ በኋላ ራእይ ፓርቲ ገብተው ሲያንጎዳጉዱ የነበረ÷ አሁን ከአቶ አበባው ጋር በመኢአድ የሚያነኩሩ ዋና ተሰላፊ ናቸው) ÷…ትክክለኛ አባላቱ ገብተው በተመረጡ ‹ሽማግሌዎች› አማካኝነት የተከሰተው ችግር በጭዋነት ተወያይተው ይፈታል ተብሎ በመታመኑ፡- ወ/ሮ ሳባ መኮንን የመአሕድ/መኢአድ መስራችና ታጋይ በቦታው በመገኘት፣ በምርጫ ግርግር ልጃቸው የሞተባቸው ወ/ሮ ይታይሽ አያሌው ድፎ ዳቦ ይዘው በመምጣት፣ ታህሣስ 17 ቀን 2003 ዓ. ም በጠቅላላ ጉባኤው ወቅት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በኢ/ር ሀይሉ ጉልበት ላይ በማስቀመጥ የተፈጠረው ችግር ሳይፈታ የት ነው የሚሄዱት ያሉት(ዛሬ ላይ ሞቸ በነበር ብለው የሚፀፀቱ) አቶ ነብዩ ዓለምይሁን ከስምምነቱ በኋላ ሁሉም አባላት የሚደርስ ጧፍና ሻማ ይዘው በመምጣት፣….ሌሎችም ነባር አባላት ተገኝተው እያለ ነው ከላይ በተጠቀሱት ‹አመራር › ተብየዎች ሊከሽፍ የቻለው፡፡ በእለቱ ቁጥሩ የበዛ ‹ደህንነት›፣ ፖሊስ፣ ኢዜ..አ….በጽ/ ቤቱ ዙሪያ ከበው ጉዳዩን ሲከታተሉ ነበር፡፡
መኢአድ ለአለፉት 3ዓመት ከ8 ወር ከ5 ቀን ወይምለ1349 ቀናት ከ18 ስዓትት ወይም ለ80,445 ሠዓታት ከማባከኑም በላይ ፤ የምዕራብ በለሳ የ2002 የተወካዮች ም/ ቤት ዕጩ አቶ ምሳው ዮሐንስን ጨምሮ ከማእከል 4 አባላቱን በወያኔ ገዳዮች በማስገደል፣ አቶ ብርሀኑ አባሆይን በመጥረቢያ ወገቡን በማስመታት፣….ቁጥሩ የበዛ አመራሩና አባላቱን በማሳሰርና በማስደብደብ፣…ለዘርፈ ብዙ ችግር የተጋለጠ፣ 2 በኢየሩሳሌም ሆቴልና በዋናው ጽ/ ቤቱ ያልተገባ ጠቅላላ ጉባኤ‹አድርጌአለሁ› ብሎ ብዙ ገንዘብ ያባከነ፣ በጽ/ ቤቱ ውስጥ ላሉት የወያኔ ደህንነቶች ወርሀዊ ደሞዝና አበል የሚከፍል፣ የበርካታ አባላቱንና የህዝቡን ምስጢር ለወያኔ እያሰጠ በራሱ ላይ ችግር የሚያደርስ(ገዥው ፓርቲ የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ 99% በእጃችን ነው ይላል)፣…..እቶ ያእቆብ ልኬ፣ አሰፋ ሀ/ ወልድ፣ አበባው መሀሪ፣….የተባሉ ፎርጅድ ‹መሪዎችን› በኢ/ር ሀይሉ ፈቃጅነት ባልተሟል ጉባኤ መርጫለሁ ብሎ እየዳከረ፣ ….የሚገኝ ፓርቲ ነው፡፡
ይሁንና በጠናካራ አባላቱ፣ አመራሩ፣ ደጋፊውና፣…..በሚቻለው መጠን ወደነበረበት ለማስመለስ ጥረትና ተጋድሎ እየተካሄደ ነው፡፡
አንድ ሊገነዘቡት የሚገባ አብይ ነገር ግን ለሚባክነው፡- ጊዜ፣ ጉልበት፣ የሰውኃይል፣ ገንዘብ፣ ውድ የቅስቀሳ ሥራዎች፣ በአባላቱና በአመራሩ ለደረሱትና ለሚደርሱት ማናቸውም ነገሮች፣…..ሁሉ አቶ አበባው(ኢ/ር ሀይሉ)እና በስራቸው ያሉት ወያኔዎች የሚያወራርዱት መሆኑን እንዲያውቁት የእምየ ኢትዮጵያ ቁርጥ ልጆች አበክረው ያሳስባሉ!!! በሕይወት፣ በደም፣ በሀገርና በሕዝብ፣ በገንዘብና በጊዜ ላይ የሚቀልዱት፣…. ሁሉ ‹‹ዝም›› ተብሎ የሚታለፍ አይደለም!!!
ርእየ- ሁለንተና             « ታምራት ይደጎ »
13/ 12/ 2006 ዓ. ም
አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ

Friday, August 1, 2014

አቶ በረከት ከሆስፒታል ወጥተው ወደ አልታወቀ ስፈራ መወሰዳቸው ተገለፀ

ሰሞኑንን ጅዳ ሳውዲ አረቢያ አንድ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ የነበሩት አቶ በረከት ስሞኦን ሞቱ እይተባለ የሚናፈሰው ዜና ትክለኛ አለመሆኑን የሚገልጹት ምጮች ። የመንግስት ባለስልጣኑ ዛሬ ማምሻውን ከሆስፒታል ወጥተው ሼክ አላሙዲን ወደ አዘጋጁላቸው ሆቴል «ማረፊያ» ማቅናታቸውን አረጋግጠዋል። 
እሁድ ለሊት በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን ሳውዲ አረቢያ ለህክምና በሚስጠር የገቡት እኚሕ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የልባቸውን የደም ቧንቧ ለማስፋት የተደረገው ህክምና ስኬታማ እና ለክፉ ችግር የማይሰጣቸው መሆኑን የሆስፒታሉ ምንጮች ቢገልጹም የባለስልጣኑ የሰውነት አቋም ከትጎሳቀለው እና ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የጠቆረው ፊታቸው ገጽታ ሰውነታቸው ውስጥ መልካም ነገር እንደሌለ ያመላክት እንደነበር በአካል ያዮቸው የአይን እማኞች አቶ በረከት በቀርብ ቀን ወደ ሃገር ቤት አሊያም ለተሻለ ህክምና ወደ አውሮፓ ለማቅናት እቀድ እንዳላቸው ገልጸዋል። ዛሬ ረፋዱ ላይ አቶ በረከት ከሚያገግሙበት ሆስፒታል ለቀው ከመውጣታቸው ቀደም ብሎ ለጉብኘት ወደ ሆስፒታሉ አቅንተው የነበሩ ምንጮች በአካባቢው ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳልነበረ እና ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ እንዳልቀሩ የሚገመቱ ነጭ ለባሾች ሆስፒታሉ አካባቢ መታየታቸውን አረጋግጠዋል፡፤ 
ይህ በዚህ እንዳለ ከአቶ በረከት ስሞኦን ጋር የመጡት የጦር ሃይሎች ሆስፒታል ዶ/ር ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ በዝግጀት ላይ መሆናቸውን እነዚሁ ምንጮች አክለው ገልጸዋል። ። የአቶ በረከት ስሞኦን የጤንነት ሁኔታ በተመለከት ከጅዳው የኢትዮጵያ ቆንሳል ጽ/ቤት መረጃ ለማግኘት ያድረኩት ሙከራ ባይሳካም ለዕረፍት ሀገርቤት የሄዱትን ቆንስላ ሸሪፈን ተከተው ወ/ሮ ሙንተሃ ወደተጠቀሰው ሆስፒታል ሰው እየላኩ የኚህን ባለስልጣን የጤነነት ሁኔታ በቀርብ በመከታተል ላይ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። 
ባለስልጣኑ የሚገኙበትን የጤና ሁኔታ ካረፉበት ሁቴል የምናገኘውኝ መረጃ እይተከታተለን ለማቅረብ ይሞከራል Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ