

ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እረፍ ሲነሳው የከረመውን የሃስተ ክስ ለማጣራት መደበኛ ስራውን አቋርጦ ዛሬ እሁድ ለ31/8/2014 ማለዳ ደግሞ ፍ/ቤት ቢቀርበም ተመሳሳይ መልስ ስለተሰጠው ጥሪውን ወዳ ስተላለፈለት በተለምዶ ሽማልያ ስለላ የሚባል ፖሊስ ጣቢያ በማቅናት ሪፖርት ቢያደርግም ተረኛ የሳውዲ ፖሊስ መኮንኖች ስለጉዳይ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው ጋዜጠኛውን በነጻ እንዳሰናበቱት ለመረዳት ተችሏል ። ጋዜጠኛ ነበዩ ሲራክ በማለዳ ወጎቹ ያቀርባቸው በነበሩ አሳዛኝ እና አሰቃቂ የእቶቻችን የአረበ አለም ህይወት ገጽታ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ዘንድ አድናቆት እና ክበርን ያተረፈ ታላቅ ግዜጠኛ መሆኑ ቢታወቀም በዚህ ስራው ባልተደሰቱ ምስለኔዎች ቀደም ብሎ በቀረበበት የሃሰት ከስ ለእስር ተዳርጎ እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች ጋዜጠኛውን በእጅ አዙር ለማዋከብ የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል ሊሆን እንደሚቸል ይናገራሉ። ይህ ጋዜጠኛ በወቅቱ በተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶች እና የኢትዮጵያ ህዝብ ተዕጸኖ ነጻ ቢወጣም በአረብ አለም ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ምን አይነት ዘጋባ እንዳያቀረብ በተላልፈበት ከባድ ማስጠንቀቂያ ከጀርመን ድምጽ ዘጋቢነቱ በመራቅ እስካሁንም የህሊና እረኛ መሆኑን ይናገራሉ ።
በአሁኑ ግዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ ስለሚፈጸመው ግፍ እና በደል መናገር ወንጀል ሆኗል የሚሉት ምንጮች ። በተለይ በኮንተራት ሰራተኛ እህቶቻችን ሬሳ ዶላር የሰበሰቡ አንዳንድ የአሰሪ እና ሰራተኛ ኤጀንሲ ባለቤቶች ሃላፊነት የማይሰማቸውን ደካማ የመንግስት ባለስልጣናት እንዳሻቸው እያሸከረከሩ በወገኖቻችን ላይ ስለሚደርሰው ግፍ እና በደል በአደባባይ በሚናገሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ ተጸዕኖ ማሳደር መቻላቸውን ይገልጻሉ። እንዚህ ምንጮች አያይዘው ሲገልጹ ምን እንኳን በኮነትራት ሰራተኛ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ግፍ እና በደል ሃገር አቀፍ ተቃውሞ በማስነሳቱ መንግስት ከግል ጥቅማቸው ባሻገር የወገኖቻቸው ህይወትን ማየት በተሳናቸው የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ላይ በወስደው አንጻራዊ እርምጃ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ህይወት ከስቃይ መታደግ ቢቻልም እነዚህን ወንጀለኞቸ ለፈርድ በማቅረብ ረገድ የውጨ ጉዳይ ሚንስተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ገብተው የነበረውን ቃል ማጠፋቸው ግፉ የተፈጸመበትን ድፈን የኢትዮጵያን ህዝብ እጀግ በጣም አሳዝኗል ብለዋል:: እንደሚታወቀው በተጠቀሱት ኤጀንሲዎች አማካኝነት ሳውዲ አረቢያን ጨምሮ ወደ ተለያዩ አረብ ሃገራት በኳንተራት ቪዛ ገበተው ያሉበት ሁኔታ እሳክሁን በወል ከማይታወቀው በመቶሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ባሻገር በሰው እጅ ተገለውም ሆነ በተለያየ ምክንያት ህይወታቸው አጥተው የኤንባሲ አሊያም የቆንስላ ባለስልጣናት ለወላጆቻቸው ሳያሳውቁ መርዶ ነጋሪ በሌለበት አረብ በረሃ ስረአተ ቀብራቸው የተፈፀመ እህቶቻችን ማንነት በሚስጠር መያዙ ይነገራል።
ምንጭ Ethiopian Hagere Jed Bewadi
No comments:
Post a Comment