ኢትዮጵያን ሀገሬ ጅዳ በዋዲ
ከሁለት ሳምንት በፊት « ወገኔ በልስማኝ ሃገሬ አንድነት ይብጀናል ዛሬ » በሚል ነጠላ ሃገራዊ ዜማው የተደናገጡ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ መንግስት ድህንነት አባላት ክተትል ይደረግበት የነበረው ድምጻዊ ብረሃኑ ተዘራ ሰሞኑንን ወደ አሜሪካ ማቅናቱን ለማወቅ ተችሏል። የህዝብን ፍላጎት በሆነ ነገር በመጨበጥ መግታት እንደ ማይቻል የሚናገረው ድምጽዊ ብርህኑ ተዘራ በተለይ ከኢሳት ድምጽ ጋር ሰሞኑን ባደረገው ቃለ ምልልስ ሲገልጽ « በመንግስት የተከለከለ አንድ ነገር በህዝብ ዘንድ ተቀባይነት እንዳለው በመጥቀስ ህዝቡ በተቃራኒ ጎራ መቆሙን አውስቷል ይህንንም ተከትሎ ሃገራዊ አንድነትና እውነታን ማንም መገደብ ስለማይቸል « ወገኔ በልስማኝ ሃገሬ አንድነት ይብጀናል ዛሬ » የሚል ነጠላ ዜማው ወቅታዊና የህዝብን ስሜት የሚገልጽ በመሆኑ በኢትዮጵያውያን ዘንድ በከፍተኛ ደረጃ ተደማጭነትን
ማግኘቱን አክሎ ገልጾል፡ በዚህ ነጠላ ዜማ ውስጥ
« አይደለም አየሩ አይደለም ተራራው ፣
ሲርብ የሚያበላው ሃገር ማለት ሰው ፣
ለሆዱ ያደረ ወዳጁን የረሳ ፣
ነፃነት ምኑ ነው ቢነገር ቢወሳ ፣
» በሚለው የስንኝ ቋጠሮ የተበሳጩ የኢ.ህ.አ.ዴ.ግ ካድሬዎችና ቱባ ባለስልጣናት አርቲስቱ በኢትዮጵያ ህዝብ ዘንድ ተደማጭነት ካለው የኢሳት ድምጽ ጋር ቃለ ምልልስ በማድረጉና ዛሬ አሌክስ አንደር ቨሪጂንያ ውስጥ የህዝብን ትግል መቀላቀሉን በሚያበስረው ዝግጀት በአሁኑ ግዜ ጥላቸውን በማያምኑ የመንግስት ሃይሎች ጥርስ ውስጥ የገባው አርቲስት ወደ ሃገር ሲመለስ ወከባ ሊፈጸምበት እንደሚችል ምስጢራዊ ምንጮች ይገልጻሉ። በአጭር ግዜ ውስጥ የአብዛኛውን ኢትይጵይዊ ትኩረት የሳበው የአርቲስት ብረሃኑ ተዘር ነጠላ ዜማ ኢትዮጵያ በመዲናይቱ አዲስ አበባና በተለያዩ ክፍለ ህገራት ምግቤቶች ቡና ቤቶችና የትራንስፖርት አገልግሎት መስጫ ተሽክርካሪዎች ውስጥ ጭመር ሳይቀር በስፋት በመደመጥ ላይ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡
«ወገኔ በልስማኝ ሃገሬ፤
አንድነት ይበጀናል ዛሬ ፤
መቼም አይሻረም ኢትዮጵያዊነቱ፤
መኖር ግን አይሻም ያለነጻነቱ ፤
እኮ ! ማነው ሰጪ ማነውስ ከልካይ፤
ሰው እንዳሻው ቢኖር በሃገሩ ላይ ፤
እያለ የሚያዜማው ድምጽዊ ብርሃኑ ክኢስት ለቀርበለት ጥያቄ አያሌ የሃገር ፍቀር ዘፈኖችን እንደዘፈነ ግልጾ ወገኔ በልስማኝ ሃገሬ የሚለውን ነጠላ ዜማ ከለቀቀ ወዲህ በከፍተኛ ደረጃ ይህዝብን ተኩረት ማግኘቱ አግርሞትን እንደ ደጫረበት በመናገር ከአቅሙ በላይ የሆኑ ምስጋናዎች ከህዝብ ስለተቸረው በህዝብ ውስጥ ያለውን እውነታ በሙያው ማንጸባረቅ በመቻሉ መደሰቱን ገልጾ ክብርና አድናቆትን ለቸሩት ሀገር ውስጥና በውጭ ሃገር ለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ሁሉ ከልብ የመነጨ ምስጋናውን አቅርቧል ። ድምጻው ብረሃኑ ተዘራ ዛሬ በአሜሪካ ቨርጅኒያ ግዛት ውስጥ አዲስ ያወጣውን ነጠላ ዜማ ሲዲ በነጻ እንደ ሚያድል ለመረዳት ተችሏል፡ ይህ በዚህ እንዳለ ከዝግጀቱ በኃላ አርቲስት ብረሃኑ ወደ ህገር ይመለስ አይመለስ እስካሁን በግልጽ የተባለ ነገር ባይኖረም ምናልባት ከመንግስት ጥቃት እራሱን ለመከላከልና በነጻነት ለመኖር አርቲስቱ የሌሎች የህዝብ ትግል አጋሮቹን ፈለግ ሊከተል ይችላል ተብሎ ይታመናል። Ethiopian Hagere Jed bewadi
No comments:
Post a Comment