በዚህ ፕሮግራም ላይ የተገኙት የመግስት ልኡካን ቡድን መሪ የወገኖቻችን ህይወት አሳስቢ መሆኑን ገለጹ ።
=======================================================
በሳውዲ አረቢያ ሪያድ የመንፉሃን ሁከት ተከትሎ በቅርቡ ወደ ሳውዲ አረቢያ ያቀናው የመንስት ሎኡካን ቡድን በየመጠለያው እና በየእስርቤቱ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን ህይወት አስከፊ ሁኔታ ውስጥ እንዳለ ሳይሸሽጉ የአይን ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል ። ወገን ለወግን ደራሽ ወገን ነው በሚል ኖቬብር 29 2013 ምሸት በሳውዲ አረቢያ ሪያድ ከተማ ከስደት ወደ ሃገራቸው ተመላሽ ወገኖቻችን ድጎማ የሚውል የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም ላይ ከህዝብ ጋር ለመጀምሪያ ግዜ ሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ እንድተገኙ የሚነገርላቸው የመንግስት ሎኡካን ቡድን ተወካዮች በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ወገኖቻችን ላይ እየደርሰ ያለው ስቃይ እና በደል ከመቸውም ግዜ በላይ አስቃቂ እየሆነ መምጣቱን በወቅቱ ለነበሩ ታዳሚዎች ባድረጉት ነግግር መናገራቸውን ምንጮች ገልጸዋል።

በተለያዩ የመጠለያ ጣቢያዎች የሚገኙ ኢትዮጵያውያንን ተዘዋውረው መጎብኘታቸውን በንግግራቸው ላይ የገለጹት የመንግስት ልኡካን ቡድን ተጠሪ አንባሳደር ውብሸት አባዛኛው ወገኖቻችን ያሉበት ሁኔታ አሳዛኝ እና ልብ የሚነካ ከመሆኑም በላይ ሴት እቶቻችን እና ህጻናት ልጆቻቸው በመጸዳጃ ቦታ እና በፓፐርስ እጦት ንጽህናቸውን መጠበቅ ያልቻሉበት ሁኔታ እና ከቁጥጥር ውጭ የወጣ መሆኑን ተናግረዋል። ሚንስትሩ አክለው ሲገልጹ በአንድ የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ባለው ትርምስ ወደ ሳውዲ አረቢያ ከገባች 3 ወር ያልሞላት የኮንሷ ብሄረሰብ ተወላጅ ኢትዮጵያዊት ወጣት ችግሯን በአረብኛ ወይም አማርኛ ቋንቋ መግለጽ ተስኖዋት ሌሎች ወገኖቿ ሊረዳዎት በማይችሉ የትውልድ ቋንቋዎ እይተናገረች ስቅስቅ በላ ስታለቅስ መታዘባቸውን ልብ በሚነካ አቀራረብ ለተሰብሳቢው በማስረዳት ወገኖቻችን አሁን ሳውዲ አረቢያ ስላሉበት ፈታኝ እና አስቃቂ የመከራ ግዜ አፋጣኝ ትኩረት ሊሰጠው የሚገባ ጉዳይ ነው ብለዋል።
በሳውዲ አረቢያ ወደ ሃገሩ መግባት የሚፈልገው ኢትዮጵያዊ ቁጥር ከግዜ ግዜ እየጨመረ መምጣቱን ተከትሎ የሳውዲ አረቢያ እስርቤቶች በመሙላታቸው ለደህነቱ ዋስትና ያጠው ህዝባችን ከቤት ንብረቱ በመፈናቀል በየግዜያዊ መጠለያ ጣቢያ ያለበቂ ምግብ ወሃ እና መስረታዊ ፍጆታ እየተሰቃየ እንዳለ እና ወደ ሃገሩ ለመግባት በሚያደርገው ቆይታ የከፋ እና አሰቃቂ አደጋዎች ሊገጥሙት እንደሚችል በማውሳት ለወገኖቻችን ትኩረት ሰጥቶ የህዝባችንን ህይወት ለመታደግ መረባረብ የሚገባን አሁን ነው ብለዋል። ይህ በዚህ እንዳለ ሰሞኑን በውጭ ጉዳይ ሚንስቴር ቃላ አቀባይ አንባስደር ዲናሞ ሙፍቲ በሳውዲ አረቢያ ወገኖቻችን ላይ እየደረስ ያለውን ችግር አስመልክተው የሚጋነን እንዳልሆነ በማጣጣል የሰጡትን ጋዜጣዊ መግለጫ የሪያድ ነዋሪዎች የመረጃ እጠረት ያለበት እና በግል ስሜት የተነገረ መሆኑን በማስታወስ በነ አንባሳደር ዲናሞ አይነት ለዜጎች ህይወት ዴታ በሌላቸው ደካማ የመንግስት ባለስልጣናት ሀገሪቷ መመራቷ ወደፌት በጣም አሳሳቢ መሆኑን ተናግረዋል።

ትላንት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ በተደረገ በዚህ ጥቂት የልማት ማህበር አባላት እና ደጋፊዎቻቸው ጨምሮ አንዳንድ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግርም ላይ የመድረኩ መሪ በውጭ ሃገር የሚኖሩ ወገኖቻችን በሃይማኖት በብሄር በቋንቋ ሳይለያዩ በአንድ ድምጽ አደባባይ በመውጣት በሳውዲ አረቢያ መንግስት ላይ ላደረጉት ጫና መስጋና ሊቸራቸው እንደሚገባ የገለጹበት አጋጣሚ በደማቅ ጭብጨባ እና ሆታ ለደቂቃዎች የአዳርሹን ድባብ ለውጦት እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች አንባሳደር ውብሸት በውጭ የሚኖሩ ፀረ ሰላም ሃይሎች ብለው እንዚህን ወገኖቻችንን በመፈረጅ መንግስታቸው ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው ጸረ ሰላም ድርጊት እያካሄዱ ያሉትን ቅጥረኞች በቅርብ እይተከታተሉ መሆኑንን በመግለጽ ከመደርክ አስተባባሪዎቹ አድናቆት የተቸራቸውን የኢትዮጵያውያን ወገኖቻችንን እንቅስቃሴ በማውገዝ ታዳሚውን ክፉኛ አሳዝነዋል።
በወቅቱ አንዳንድ ወገኖች መድረክ አጊተው እንደነበር የሚናገሩ ምንጮች አንድ የህገር ሽማግሌ አባት የገቢ ማሰባሰባሰቢያ ፕሮግራሙን የተቀደሰ አላማ በማለት ገልጸው ሁላችንም ኢትዮጵያውያን ነን ዛሬ የሳውዲዎቹ ጥቃት ያነጣጠረው መኖሪያ ፈቃድ በሌለው ወገኖችን ላይ ብቻ ሳይሆን የሃበሻ ደም ባለው ላይ ሁሉ ስለሆነ መንግስት ለደህነታችን ዋስትና ምን እየሰራ ነው በሚል ለልኡካን ቡድኑ ያቀረቡላቸው ጥያቄ ተድበስብሷ እንደታለፈ ገልጸዋል ። ጉዳዩ በብሄራዊ ደረጃ መታየት እንደሚገባው የሚናገሩ ኢትዮጵያውያን የሪያድ ነዋሪዎች በወገኖቻችን ስም በየጓሮው ያለ ደረሰኝ የሚሰብሰበው ገንዘብ አሁን ሪያድ ውስጥ ላለው ወገናችን በምንም አይነት መልኩ ሊደርስ እንደማይችል ገልጾው ገንዘቡ የስደተኞቹን ጉዳይ ለመስፈጸም የጸህፍሀት መስሪያዎች እና መሰል ተዛማጅ ነገሮች የገንዘብ እጥረት አለብን እያሉ ለሚያዛጉት በሪያድ የኢትዮጵያ መንግስት ዲፕሎማቶች ኪስ ማደለቢያ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።
በስልክ ያነጋገርኳቸው አንድ ሪያድ ከተማ የሚኖሩ የሃይማኖት አባት በበኩላቸው ገቢ በማሰባሰቡ ጽንሰ ሃሳብ ላይ ተቃውሞ እንደሌላቸው ተናግረው የወገኖቻችንን ህይወት ለመታደግ ለአለም አቀፍ የዕርዳታ ድርጅቶች በዚህ ዙሪያ ተሳታፊ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ መንግስት ጠንክሮ መስራት እንደሚገባው እና ከሰደት ተመላሽ ወገኖቻችንን ለማቋቋም ካሰፈለገ በብሄራዊ ደረጃ ህጋዊ በሆነ መንገድ የገቢ ማሰባሰቢያው ፕሮግራም መደረግ ተገቢ መሆኑን መክረው አሁን በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ በዲፕሎማቱ እየተድረገ ያለው የገበያ ግርግግር የተለመደ በመሆኑ በአብዛኛው ህዝብ ዘንድ ተቀባይነት የለውም ብለዋል። በወገኖቻችን ስም በሚደረግ በዚህ የገቢ መሰባሰቢያ ፕሮግራም በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ት/ቤት 2 ሺህ ተማሪዎች ከያንድንዱ 10 ሳ ሪያል ለመሰብሰብ ዲፕሎማቱ እቅድ መያዛቸውን የሚገልጹ ምንጮች አርብ ምሽት በተድረገው ፕሮግራም ከልማት ማህበራት ከእድሮች ከኮሚኒቲው ማህበር እና ጉዳዩ ካልገባቸው አንዳንድ ወግኖች እስከ 3 መቶሺህ ሪያል በወገኖቻችን ስም መሰብሰቡን ለመረዳት ተችሏል ብለዋል።
በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳርሽ እንደዚህ አይነት የግቢ መሰባሰቢያ ፕሮግራም ሲደረግ ለሁለተኛ ግዜ መሆኑን የሚናገሩ ወገኖች ቀደም ሲል ላለፉት 11 ወራት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ አነስተኛ ኮንቴነር ውስጥ በር ተቆልፎባቸው ሲሰቃዩ ለነበሩ 12 ነፍሰጡሮችን ጨምሮ ከ200 ለሚበልጡ እህቶቻችን የአይሮፕላን ትኬት መግዣ ፤ በተዘጋጀ የግቢ ማሰባሰቢያ ፕሮራም ላይ እስከ 1መቶ ሺህ ሪያል « ግማሽ ሚልዮን ብር » ተገኝቶ እንደበር በማስታወስ የተጠቀሰው ገንዘብ ለታቀደለት አላማ ሳይውል በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ መጠለያ ውስጥ የነብሩትን ወገኖቻችን ስበዕና ያልፈጠረባቸው በነዚህ አረመኔ ዲፕሎማቶች ለሳውዲ አረቢያ ፖሊስ ተላልፈው በመስጠታቸው ለከፋ ችግር እንደዳረጓቸው ገልጸዋል። እነዚህ የሪያድ ምንጮች አክለው ሲገልጹ የተጠቀሱት ወገኖች ለረጅም ግዜያት የሪያድ ኮሚኒት ግቢ ሲሰቃዩ የነበሩ መሆናቸው ግምት ውስጥ ገብቶ ከህዝብ በተሰብሰብው ገንዘብ የአይሮፕላን ትኬት ቀርቦላቸው በክብር ለሃገራቸው መብቃት ሲገባቸው በገዛ ዲፕሎማቶቻችን እንደዚህ አይነት ኢሰባዊ ድርጊት መፈጸሙ በምድርም በሳማይም የሚያስጠይቅ ወንጀል መሆኑን በምሬት ይገልጻሉ።
ይህ በዚህ እንዳለ ቀደም ብሎ በኢትዮጵያውያኑ ስም የተሰበሰብው 1 መቶ ሺህ ሪያል ወይም « ግማሽ ሚልዮን ብር » ዲፕሎማቱ ኪሳቸው መክተታቸውን የሚናገሩ ወገኖች 12 ነፍሰጡሮችን ጨምሮ እስከ ከ200 የሚጠጉ ወገኖቻችንን በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት ጊዚያዊ መጠለያ በኖሩባቸው ግዜያቶች ከኮሚኒቲው ካፍቴሪያ እየወስዱ ሲበሉ ለከረሙት ቀልብ ወሃ እና መብራት ሂሳብ መወራረዱን ዲፕሎአምቱ በድፍረት መናግራቸው በጣም እንዳሳዘናቸው ጠቅሰው « ውሻ በላበት አፉ ይጮሃ እንዲሉ» እንዚህ አረመኔ በሪያድ የሚኖሩ ዲፕሎማቶች ሰሞኑንን በዚሁ አዳርሽ ለሁለተኛ ግዜ ያለደረስኝ ሲሰበሰብ የከረሙት 3 መቶ ሺህ ሪያል ወይም « 15 ሚልዮን ብር » ለስደተኛው ወገናችን በቀጥታ መድረሱን እንጠራጠራለን ብለዋል ።
Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ
No comments:
Post a Comment