Saturday, April 12, 2014

ጉንፋን መስል ገዳይ «የኮሮና Corona ቫይረስ» ስጋት በሳውዲ አረቢያ ::



የሳውዲ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር ጅዳ ከተማ ውስጥ 11 ስዎች በጉንፋን መስል አደገኛ ተላላፊ «የኮሮና Corona ቫይረስ» መለከፋቸውን ገለፀ።

የሳውዲ ጤና ጥበቃ ሚንስቴር ተወካይ / ዚያድ ትላንት ሃሙስ Apr 10 2014 ለሃገሪቱ መገናኛ ብዙሃን በስጡት መግለጫ ጅዳ ከተማ ውስጥ 11 የቫይረሱ ተጥቂዎች መገኘታቸውን ጠቅሰው ባለፈው አመት ሪያድ ከተማ ላይ ከተመዘገበው የበሽተኞች አሃዝ የበለጠ በመሆኑ ቫይረሱ በመላ ሀገሪቱ በስፋት ሳይስራጭ እንዳልቀረ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

/ ዚያድ በማከል ቫይረሱ ማስነጠስ የሰውነት መገጣጠሚያዎች ላይ ቁርጥማት የጡንቻ መዛል እና አልፎ አልፎ ከፍተኛ የሆነ የሰውነት ትኩሳት እንደሚያሳይ ስለበሽታው አስከፊነት በማብራራት እንደዚህ አይነት የህመም ምልክቶች የታዩበት ማንኛውም ሰው አቅራቢያው ወደ ሚገኝ ጤና ጣቢያ ቀርቦ በአፋጣኝ ምርመራ እና ህክምና ማድረግ እንደሚገባው አሳስበዋል።


በዋንኛነት የመተንፈሻ አካልን እንደሚያጠቃ የሚነገርለት ይህ ክትባት ያልተገኘለት አደገኛ ጉንፋን መስል ገዳይ በሽታ «ኮሮና Corona » እስካሁን በአለማችን ላይ የተከስተው በሳውዲ አረቢያ እና ፈረንሳይ ብቻ መሆኑን የሚገልጹ የዘርፉ ባለሙያዎች ቫይረሱ ከሰው ወደ ሰው « በማስነጠስ እና በማሳል » በትናፋሽ አማካኝነት በቀላሉ የሚተላለፍ በመሆኑ በበሽታው የተለከፍው ታማሚ የሃኪም ምከር እና የቅርብ ከትትል ካላገኝ ቫይረሱ እስከ ሞት ሊያደርስው እንደሚችል ይናገራሉ።



ሳውዲ ውስጥ ተከሰተ በተባለው በዚህ አዲስ ጎንፋን መስል «የኮሮና Corona »ቫይረስ የተጠቃ ኢትዮጵያዊ እንደሌለ ቢታወቀም ስለበሽታው በሚገባቸው ቋንቋ መረጃ ሊደርሳቸው የማይችሉ በቤት ሰራተኝነት የተሰማሩ እህቶቻችን እና ሌሎች ወገኖች ከበሽታው እራሳችውን መታደግ ይቻላቸው ዘንድ ከወዲሁ ጥንቃቄ መውሰድ ይጠበቅባቸዋል።

Ethiopian Hagere ጅዳ በዋ

No comments:

Post a Comment