Monday, October 14, 2013

የኢትዮጵያን ፖሊስ ሰራዊት ግንባር ቀደም በሃላፊነት የሚያስጠይቅ አስቃቂ የግድያ ወንጀል «በጅማ ከተማ» ።


         የጉዞ ትዝብት ! ፖሊሳዊ ክህሎት እና ንቃት የሌለው የፖሊስ ሰራዊት በኢትዮጵያ !




ፖሊስ በህዝብ እና በሃገር ድህነት ላይ የሚደርሱ አደጋዎች ቀደሞ ብሎ የማምከን ግንባር ቀደም ሃልፊነት እና ግዴታ እንዳለበት  ማንም ሊክደው የማያችል እውነታ ነው። ይህን እውነታ መተግበር እየተሳነው የመጣው የኢትዮጵያ ፖሊስ አልፎ አልፎ ከህዝብ የሚቀርቡለትን መረጃዎች መተግበር  ተስኖት በተዘዋዋሪ ሰላሜን ጸጥታዬን ያስጠብቅልኛል ብሎ ተስፋ በጣለበት ህዝብ ላይ የወንጀል ድርጊት የሚፈ ተባባሪ እየሆነ መምጣቱ ለፖሊስ ሰራዊቱ ሌላ የሰለጠነ ብቃት ያለው የፖሊስ ሃይል እንደሚያስፈልገው ሃገራችን ውስጥ በተደጋጋሚ በፖሊስ ሰራዊቱ እንዝላልነት የሚከሰቱ ወንጀሎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ያመለክታሉ ።


የጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ሰሞኑንን የ3 ህጻናት ወላጅ የሆነችውን ባለቤቱን በአሰቃቂ ሁኔታ በስለት ወግቶ የገደለውን አባወራ የምርመራ ውጤት እንደ ጀብዱ ሊያስደምጠን የሞከረው የኢትዮጵያ ፖሊስ ቴሌቪዥን ፕሮግራም ስርጨት በግናብር ቀደም መጠየቅ የሚገባቸውን የሰራዊቱን አባላት ያፈጠጠ ስህተት ለማድበስበስ በተጠቀሰው ወረዳ የፖሊስ ምርመራ ውጤት የህዝቡ ቀልብ ለመሳብ ሲያስደምጠን በነበረው ትረካ  « የዝግጀት ክፍሉን አላውቂ ሳሚነት ለመረዳት ይግድ ነብይ መሆን አያሻም።  አዎ « ፖሊስ በቡድን እና በተናጥል የሚፈጸሙ ወንጀሎችን ቀድሞ የመከላክል ሃልፊነት እና ግዴታ አለበት  » የሚለውን እውነታ በቅጡ መገንዘብ የተሳናቸው  የማስታውቂያ ሚንስቴር የሞቀ ህንጻ ላይ ተኮፍሰስው በስማ በለው ያረቀቁትን ልብወለድ በሳምንቱ መጨረሻ «እሁድ» የሰራዊቱን ፋቲክ ተጀቡነው እንደገደል ማሚቱ የሚያስተጋቡትን  የዝግጀት ክፍሉን ጋዜጠኞች የሙያ ብቃት መቃኘት ይግድ ቢሆንም ዝግጀት ክፍሉ ቀጣይ ዝግጀቶች እናድሉት ስለገለፀ ……. ስለተፈጸመው ወንጀል እንደሚከተለው  ለማቋደስ ወሰንኩ ።
ታሪኩ እንዲህ ነው ። ቀኑ በጅማ ከተማ የወረዳ 2 ነዋሪ የዕለት እተዕለት እንቅስቃሴውን ለመጀምር በማለዳ ተነስቶ ጉዳይ ያለው ወደ ጉዳዩ ስራ ያለው ወደ ስራው በየፊናው  የሚንቀሳቀስበት ሰአት ነው። በዚህ ቅጽበት በተጠቀሰው ወረዳ  አንድ አስደንጋጭ ዜና ተሰማ ። ከአንድ አመት በፊት በሁለት ባል እና ሚስት መሃከል በተፈጠረ አለመግባባት ባል የ3 ልጆቹን እናት የሆነች የ6 አመት የትዳር ጎደኛውን የምትሰራበት የውበት ሳሎን መዕከል ድረስ ተከታትሎ በመ ሄድ በያዘው ስለት አንገቷ ላይ 3 ቦታ ወግቷ ገድሎ መሰወሩን የፖሊስ የምርመራ ውጤት ይገልጻል።  ገና ከማለዳው የአካባውን ነዋሪ ጉድ ያሰኘው ይህ ጭካኔ የተሞላበት ወንጀል በጅማ ከተማ ለወረዳ  2 ፖሊስ ጽ/ቤት ፖሊስ ጆሮ ይደርሳል ። ጉዳዩን ለማጣራት ወንጀሉ የተፈጸመበት ቦታ ድረስ ሄደው ፎቶ ማንሳታቸውን ወንጀለኛው  ማነው ? የሚለውን ለማወቅ በአካባቢው ያገኙትን መረጃዎች አሰባሰበው  ክትትል መጀመራቸውን የሚናገሩት የወረዳው  ተረኛ መርማሪ ነፍሰ ገዳዩን በዛው ቅጽበት  እራሱን የማጥፋት ሙከራ ሲያደርግ ደርሰው በቁጥጥር ስር ማዋሉን በኩራት ይናገራሉ። ፖሊስ በተጠቀሰው ወንጀለኛ  ላይ የሚያደርገውን ምርመራ በማጠናከር ከአካባቢው ማህበረሰብ  ባገኘው መረጃ መስረት ከአንድ አመት በፊት በመሃከላቸው በተነሳ አለመግባባት በቤተሰብ ደረጃ ተሞክሮ ስላልተቻለ ላይገናኙ ተማምለው  እንደ ተለያዩ የሚገልጸው የምርመራ ውጤት  ወንጀለኛው በቁጭት የልጆቹን እናት ለመግደል ክትትል ያደርግ እንደነበር መረጃ እንደነበረው አክሎ ይገልጻል። ከዚህ ባሻገር   «ሂሩትን ገድያት ስለመጣሁ ፖሊስ ቢመጣ ያለሁበትን ቦታ እንዳትጠቁሙ ብሎ ከፖሊስ ለመስወረ እንዲተባበሩት ወንጀለኛው  ለዘመዶቹ መግለጹን ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ አባወራው ከተያዘ በሃላ በሰጠው የእምነት ክህደት ቃል የልጆቹን እናት መግደሉን ከምርመራው ውጤት ማረጋገጡን ይገልጻል ።  እዚህ ላይ ልብ ያለው ልብ ይበል  ሞች ወ/ሮ ሂሩት ቀደም ብለው ለፖሊስ የቀድሞው ባለቤታቸው ሊገድላቸው ክትትል እያደረገባቸው መሆኑን  ለፖሊስ በመግለጽ ሊፈጸምባቸው ከሚችል ግድያ እንዲታደጋቸው በተደጋጋሚ  አመልክተው እንደነበር መርማሪው ፖሊስ ሳይሸሽጉን በማን አለብኝነት   የተናገሩትን እንኳ የጅማ ህዝብ ድፍን የኢትዮጵያ ህዝብ እሁድ ረፋድ ቀን ኦክቶበር 13 2013 በተላለፈው የፖሊስ ራዲዮ ፕሮግራም በሚገባ አድምጠናል።


በጅማ ከተማ የወረዳው 2 ፖሊስ መርማሪው በማስከተል ሲናገሩ  ሞች ወሮ ሂሩት ለፖሊስ ያቀረቡትን የነብስ አድን ጥሪ በማስታወስ  ፖሊስ ባልና ሚስት የማስታረቅ እንጂ የማፋታት ስራ እንደማይሰራ ጠቅሰው «ጅብ ከሄደ ውሻ ጮህ እንዲሉ » በሞች ወ/ሮ ሂሩት የቀረበውን  የነብስ አድን ጥሪ ጆሮ ዳባ ልበስ ብለው የወ/ሮዋ ህይወት በአስቃቂ ሁኔታ ከጠፋ በኃላ ወንጀለኛውን ተከታትሎ በመያዝ  ፖሊሳዊ ግዳጃቸውን በበቃት መወጣታቸውን ይናገራሉ። ይህ አባባላቸው በከተማይቱ ጅማ ህዝብ ዘንድ ከወ/ሮ ሂሩት ግድያጋ ተያይዞ የመነጋገሪያ አጀንዳ እንደሆነ በተጨባጭ አረጋግጫለሁ፡፤ ፖሊሳዊ ብቃት በሌላቸው የፖሊስ አባላት የሚመራውን የፖሊስ የምርመራ ውጤት በኢቲቭ የፖሊስ ፕሮግራም  መነገሩ አስፋሪነቱ አጠያያቂ ባይሆንም  እንደ ጋሪ ፈረስ ለመዘገብ የደፍረው ዝግጀት ክፍሉ ጉዳዩን በስፋት ለማየት ባለመታደሉ ያሳዝናል።  በሞች ወ/ሮ ሂሩት ላይ ለተፈጸመው ወንጀል በጅማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የወረዳ 2 ፖሊስ ጽ/ቤት ቀጠተኛ ሃላፊነት እና ተጠያቄነት ሊኖርባቸው እንደሚገባ የሁሉም እምነት ነው።                                                                          « አካላዊ እና መንፈሳዊ ብቃት የሌለው ፖሊስ ሠራዊት ለህዝብ ህይወት እና ንብረት አሌንት የመሆን የሞራል ብቃት የለውም ! 


Ethiopian Hagere  ( from Ethiopia )

No comments:

Post a Comment