Monday, September 1, 2014

ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል ተሰደደ ( በጌታቸው ሺፈራው )


  • 461
     
    Shar
ብስራት ወ/ሚካኤል
በተለያዩ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች የራሱ “አዲስሚዲያ” ብሎግን ጨምሮ በተለያዩ ድህረ-ገፆች አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል መሰደዱ ታወቀ፡፡ ጋዜጠኛው ቀደም ሲል የፍኖተ-ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ፣የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ፣ በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ኢሳው መፅሔት ባልደረባና አምደኛ፤ በኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣና በቅርቡ ወደህትመት የገባው ቀዳሚ ገፅ ጋዜጣ ላይም የተለያዩ የፖለቲካ፣ ሰብዓዊ መብት ጥሰትና ማኀበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ በራሱና በብዕር ስም እንደሚፅፍ ይወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተመሰረተውና በመንግስት ከፍተኛ ቁጥጥርና ጫና ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) መስራች አባል፤ በኋላም የማኀበሩ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ በመሆን እያገለገለ እንደነበር ይታወቃል፡፡ 

ጋዜጠኛው ከዚህ በፊትም በመንግስት ደህንነት ኃይሎች በምሽት እገታ እንደገጠመው፣ ከስልክ ጠለፋ እስከ ዛቻና ማስፈራራት ይደርስበት እንደነበር ከዚህ ቀደም የወጡ መረጃዎች ቢያመለክቱም፤በተለይ ከጥቅምት 2006 ዓ.ም. ከአዲሱ ጋዜጠኞች ማኀበር መመስረት ሂደት ጀምሮ እና በሚያዚያ ወር 2006 ዓ.ም. 3 ጋዜጠኞችን እና 6 የዞን 9 ብሎገሮች በመንግስት ከታሰሩ በኋላ የመንግስት ደህንነቶች ክትትል ከበፊቱ በበለጠ ሁኔታ ተጠናክሮ መቀጠሉንና ቀጣዩ እስር እሱ ላይም ሊፈፀም እንደሚችል በመረዳት ለቅርብ ጓደኞቹ አሳውቆ ነበር፡፡ 

ብስራት ባለፈው ነሐሴ 16 ቀን 2006 ዓ.ም. አርብ ጠዋት አዲስ ባወጣው የስልክ መስመር የማዕከላዊ ስልክ ጥሪ ካስተናገደ በኋላ ለጊዜው ከአዲስ አበባ ውጭ መሆኑን በማሳወቅ ለሰኞ እንደሚቀርብ ምላሽ ከሰጠ በኋላ ባለፈው እሁድ ድንገት ሀገር ጥሎ መሰደዱ ታውቋል፡፡ 

በቅርቡ ከታሰሩት ጋዜጠኞችና ብሎገሮች የእስር ስም ዝርዝር ውስጥ የማኀበሩ አመራሮች መኖራቸውና በቀጣይም መንግስት በአመራሮቹ ዙሪያ መረጃ እየሰበሰበ መሆኑ ምንጮች አረጋግጠው እንደነበረ ይታወቃል፡፡ ቀደም ሲል የማኀበሩ ፕሬዘዳንት ጋዜጠኛ በትረ ያዕቆብ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊው ጋዜጠኛ ዘሪሁን ሙሉጌታ፣ ገንዘብ ያዥ ጋዜጠኛ ሃብታሙ ስዩም እና መስራች አባል ጋዜጠኛ ተሰማ ደሳለኝ መሰደዳቸው አይዘነጋም፡፡ በአጠቃላይ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤልን ጨምሮ በ2006 ዓ.ም. ብቻ 25 የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች ሲሰደዱ፤3 የውጭ ዜጎች ጋዜጠኞችን ጨምሮ 20 ጋዜጠኞችና ብሎገሮች ደግሞ በእስር ላይ እንደሚገኙ ታውቋል





ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ጋዜጠኛ ነበዩ ሲራክን ለማፈን የተቃጣው ሴራ ከሸፈ ።

ሳውዲ አረቢያን ጨምሮ በመላው አረብ አለም በሚገኙ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና በደል በማለዳ ወጉ መረጃዎችን በማቀበል የሚታወቀው ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በማያውቀው ጉዳይ  ተከሶ ዛሬ ፍ/ቤት መቀረቡን ውስጥ አውቂ ምንጮች ገለጹ ።      ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ኦገስት  27/8/2014 ማለዳ 4:00  በደረሰው የከስ ጥሪ የመጣውን ሁሉ በጸጋ ለመቀበል ህግ እና ስረአት አክብሮ ወደ     ፍ/ቤት መሄዱን የሚናገሩ    ምንጮች   በአካባቢው የሚገኙ የሳውዲ ህግ አሰከባሪዎች ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ተመስረተበት ስለተባለው   ወንጀል ምንም አይነት     መረጃ እንደሌላቸው አውስተው ጥሪውን ወዳስተላለፈለት ፖሊስ ጣቢያ ሄዶ ሪፖረት እንዲያደርግ መላኩን ይገልጻሉ ። 
ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እረፍ ሲነሳው የከረመውን የሃስተ ክስ ለማጣራት መደበኛ ስራውን አቋርጦ ዛሬ እሁድ ለ31/8/2014 ማለዳ ደግሞ ፍ/ቤት ቢቀርበም ተመሳሳይ መልስ ስለተሰጠው ጥሪውን ወዳ ስተላለፈለት በተለምዶ ሽማልያ ስለላ የሚባል ፖሊስ ጣቢያ በማቅናት ሪፖርት ቢያደርግም ተረኛ የሳውዲ ፖሊስ መኮንኖች ስለጉዳይ ምንም የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ገልጸው ጋዜጠኛውን በነጻ እንዳሰናበቱት ለመረዳት ተችሏል ። ጋዜጠኛ ነበዩ ሲራክ በማለዳ ወጎቹ ያቀርባቸው በነበሩ አሳዛኝ እና አሰቃቂ የእቶቻችን የአረበ አለም ህይወት ገጽታ በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ዘንድ አድናቆት እና ክበርን ያተረፈ ታላቅ ግዜጠኛ መሆኑ ቢታወቀም በዚህ ስራው ባልተደሰቱ ምስለኔዎች ቀደም ብሎ በቀረበበት የሃሰት ከስ ለእስር ተዳርጎ እንደነበር የሚያስታውሱ ወገኖች ጋዜጠኛውን በእጅ አዙር ለማዋከብ የሚደረገው ጥረት አንዱ አካል ሊሆን እንደሚቸል ይናገራሉ። ይህ ጋዜጠኛ በወቅቱ በተለያዩ አለም አቀፍ ድርጅቶች እና የኢትዮጵያ ህዝብ ተዕጸኖ ነጻ ቢወጣም በአረብ አለም ስለሚገኙ ኢትዮጵያውያን ምን አይነት ዘጋባ እንዳያቀረብ በተላልፈበት ከባድ ማስጠንቀቂያ ከጀርመን ድምጽ ዘጋቢነቱ በመራቅ እስካሁንም የህሊና እረኛ መሆኑን ይናገራሉ ። 

በአሁኑ ግዜ ሳውዲ አረቢያ ውስጥ ኢትዮጵያውያን ላይ ስለሚፈጸመው ግፍ እና በደል መናገር ወንጀል ሆኗል የሚሉት ምንጮች ። በተለይ በኮንተራት ሰራተኛ እህቶቻችን ሬሳ ዶላር የሰበሰቡ አንዳንድ የአሰሪ እና ሰራተኛ ኤጀንሲ ባለቤቶች ሃላፊነት የማይሰማቸውን ደካማ የመንግስት ባለስልጣናት እንዳሻቸው እያሸከረከሩ በወገኖቻችን ላይ ስለሚደርሰው ግፍ እና በደል በአደባባይ በሚናገሩ ኢትዮጵያውያን ላይ ከፍተኛ ተጸዕኖ ማሳደር መቻላቸውን ይገልጻሉ። እንዚህ ምንጮች አያይዘው ሲገልጹ ምን እንኳን በኮነትራት ሰራተኛ ኢትዮጵያውያን ላይ የደረሰው ግፍ እና በደል ሃገር አቀፍ ተቃውሞ በማስነሳቱ መንግስት ከግል ጥቅማቸው ባሻገር የወገኖቻቸው ህይወትን ማየት በተሳናቸው የአሰሪ እና ሰራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች ላይ በወስደው አንጻራዊ እርምጃ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ህይወት ከስቃይ መታደግ ቢቻልም እነዚህን ወንጀለኞቸ ለፈርድ በማቅረብ ረገድ የውጨ ጉዳይ ሚንስተሩ ዶ/ር ቴድሮስ አድሃኖም ገብተው የነበረውን ቃል ማጠፋቸው ግፉ የተፈጸመበትን ድፈን የኢትዮጵያን ህዝብ እጀግ በጣም አሳዝኗል ብለዋል:: እንደሚታወቀው በተጠቀሱት ኤጀንሲዎች አማካኝነት ሳውዲ አረቢያን ጨምሮ ወደ ተለያዩ አረብ ሃገራት በኳንተራት ቪዛ ገበተው ያሉበት ሁኔታ እሳክሁን በወል ከማይታወቀው በመቶሺህ የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን እህቶቻችን ባሻገር በሰው እጅ ተገለውም ሆነ በተለያየ ምክንያት ህይወታቸው አጥተው የኤንባሲ አሊያም የቆንስላ ባለስልጣናት ለወላጆቻቸው ሳያሳውቁ መርዶ ነጋሪ በሌለበት አረብ በረሃ ስረአተ ቀብራቸው የተፈፀመ እህቶቻችን ማንነት በሚስጠር መያዙ ይነገራል። 
ምንጭ Ethiopian Hagere Jed Bewadi

Wednesday, August 27, 2014

የተማሪዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል (ሥርዓቱን ለ 20ዓመት አይተነዋል መቀየር አለበት!)


የተማሪዎች ተቃውሞ ተጠናክሮ ቀጥሏል
(ሥርዓቱን ለ 20ዓመት አይተነዋል መቀየር አለበት!)
http://www.goolgule.com/university-students-protest-continues-ethiopia/

    የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው
    የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም
    የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል
    የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም

አዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ የአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ስልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡

የኢኮኖሚ እድገት

ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም “በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም” በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ “ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም” ማለታቸው ተገልጾአል፡፡

በተመሳሳይም “2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ “አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም” የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡

እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ “እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም “ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?” ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡

የባህር በር

ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እንዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል “በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው” በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡

የትምህርት ጥራት

ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ “ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም” በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም “የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም” በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡

ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ” ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡

(ምንጭ: ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ – ፎቶ ከፋይል ማህደር)


የኢትዮጵያ የባህር በር ለኤርትራ መሰጠቱ ስህተት ነው

የኢኮኖሚ እደገቱ እውነት አይደለም

የትምህርት ስርዓቱ ወድቋል
የተማረ ሰው ክብር አይሰጠውም
አዲስ አበባ ውስጥ ሳውዝ ካምፓስ (ልደታ)፣ አቃቂ (AASTU)፣ ፍቼ የግብርና ኮሌጅ፣ ስድስት ኪሎ፣ አምስት ኪሎ፣ አራት ኪሎ፣ የአዲስ አበባ የቢዝነስና ኢኮኖሚክስት ትምህርት ክፍልና ሌሎችም አካባቢዎች ከነሃሴ 15 ጀምሮ ስልጠና ላይ የሚገኙ የመጀመሪያ ዙር ሰልጣኞች ተቃውሟቸውን ማሰማታቸውን እንደቀጠሉ የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ ተማሪዎቹ ገዥው ፓርቲ አለ በሚለው እድገት፣ የባህር በር፣ የተማረው የማህበረሰብ በሚደርስበት በደል፣ የትምህርት ጥራት፣ የመምህራን የእውቀት ደረጃ ማነስ፣ ድህነትና አጠቃላይ ኢኮኖሚ ውድቀት ላይ ጠንከር ያለ አስተያየትና ተቃውሞ መሰንዘራቸውን ተገልጾአል፡፡
የኢኮኖሚ እድገት
ተቃውሞ ከገጠማቸው ጉዳዮች መካከል የኢኮኖሚ እድገት አለ የለም የሚለው ሲሆን ተማሪዎቹ ‹‹በአክሱም ዘመን ገናና የነበረችው ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት በኢኮኖሚው መስክ ጭራ›› መሆኗን በመግለጽ እድገቱ አለ መባሉ ስህተት መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ጨምረውም “በቀን አንድ ጊዜ እንኳን መመገብ የማይችል ማህበረሰብ ይዘን አድገናል ማለት አንችልም” በሚል እድገት አለመኖሩን ተከራክረዋል፡፡ “ሀገራችን ውስጥ የምግብ፣ የቤት፣ የትምህርት፣ የኔትወርክና ሌሎች ችግሮች አሉ፡፡ ስኳርና ዘይት ለመግዛት ህዝብ ቀበሌ ተሰልፎ ነው የሚውለው፡፡ በ400 ብር ደምወዝ ቤተሰብ የሚያስተዳድር ህዝብ ያለባት ሀገር የሌሎችን እድገት ፈዛ እያየች ያለችን ሀገር አድጋለች ልንል አይገባም” ማለታቸው ተገልጾአል፡፡
በተመሳሳይም “2 በመቶ የሚሆነው የአሜሪካ አርሶ አደር ዓለምን በሚመግብበት በአሁኑ ወቅት 85 በመቶ አርሶ አደር ይዘን ለምን እንራባለን?” የሚል ጥያቄ ማንሳታቸውንም የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ጠቅሰዋል፡፡ ተማሪዎቹ “አድገናል ብለን ራሳችን ማወዳደር ያለብን ከ40 አመት ከነበረ ስርዓት ጋር መሆን የለበትም፡፡ እድገታችን መለካት ካለበት ከሌሎች አገራት ጋር ነው፡፡ መካከለኛ ገቢ ካላቸው አገራት በ2020 እንመደባለን ከተባለ መንግስት መቀየር ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም ይህን ስርዓት ለ20 አመት አይተነዋል፡፡ ባለፉት አመታት ለውጥ ሊያመጣ አልቻለምና በ2020ም ለውጥ ያመጣል ብለን አንጠብቅም” የሚል ጠንካር ያለ ሀሳብም አቅርበዋል፡፡
እድገት ላይ ነው የሚባለው የኮንስትራክሽን ዘርፍ የጥራት ደረጃው ዝቅተኛ መሆኑን በተለይ በዘርፉ ትምህርታቸውን እየተከታተሉ የሚገኙ ተማሪዎች አንስተዋል፡፡ ተማሪዎቹ “እድገት የምንለው የህንጻዎችን ወደላይ ማደግ ወይንም መብዛት ሳይሆን የማህበረሰቡን አስተሳሰብና አኗኗር ዘይቤ መቀየር ነው” ሲሉ ተከራክረዋል፡፡ በስልጠናው ወቅት ገዥው ፓርቲ የቻይናን ፈለግ ተከትሎ እድገት ማስመዝገቡን በመቃወም “ቻይና ከ2.3 እስከ 2.7 በመቶ እያደገች እንደሆነ ይነገራል፡፡ የእሷን ፈለግ ተከተለች የተባለችው ኢትዮጵያ ከ11.2 በመቶ በላይ አደገች ነው የሚባለው ከየት አምጥተነው ነው? ወይስ እንደ ቀን አቆጣጠራችን እድገታችንም ይለያያል?” ሲሉም አሰልጣኖቹን ጠይቀዋል፡፡
የባህር በር
ተማሪዎቹ ለኤርትራ መሰጠቱ አግባብ እንዳልሆነ፣ የባህር በርና ወደቡ ለኢትዮጵያ ቀጣይ እድገት፣ ደህንነትና ታሪክ አንጻር አስፈላጊ መሆኑን በመግለጽ ገዥው ፓርቲ በባህር በር ላይ ያለውን አቋምና ፈጸመ ያሉትን ስህተት ተችተዋል፡፡ ወደብ አልባ በመሆናችን ኢኮኖሚያችን ወደኋላ መቅረቱንም አንስተዋል፡፡ በሌላ በኩል “በአገራችን የሚመረቱ ሰብሎችና ፍራፍሬዎች ለአገር ውስጥ ገበያ የሚቀርቡት ከውጭ ከተላከው ሲተርፍ ነው” በማለት በኤክስፖርት ዘርፍ ያለውን ችግር፣ አገር ውስጥ እየተፈጠረ ያለውን የኑሮ ውድነት ከዚሁ ችግር መመንጨቱን ጠቅሰዋል፡፡
የትምህርት ጥራት
ተማሪዎቹ የራሳቸውን ተሞክሮ በመጥቀስ የትምህርት ስርዓቱ ችግር ያለበት መሆኑን በመከራከሪያነት አቅርበዋል፡፡ “ለተማረ ሰው ክብር እየተሰጠ አይደለም” በሚል የእነሱም እጣ ፈንታ ተመሳሳይ መሆኑን ስጋታቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም “የሚያስተምሩን አስተማሪዎች የእውቀት ደረጃ ጥያቄ ምልክት ውስጥ ነው፡፡ በየ ዩኒቨርሲቲው በአመራር ላይ የሚገኙ ግለሰቦች እውቀት የላቸውም” በማለት ዩኒቨርሲቲዎች ላይ የተደቀነውን አደጋ አንስተዋል፡፡
ዲግሪ ይዘው በስራ ፈጠራ ስም በጥቃቅንና አነስተኛ እንዲደራጁ የሚደረገውን የተቃወሙት ተማሪዎቹ “የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተደራጅተው ካፌ ከፈቱ፣ ኮብልስቶን አነጠፉ ሲባል ነው የምንሰማው፡፡ ለዚህ ስራ ደግሞ ዩኒቨርሲቲ መማር አያስፈልገውም፡፡ ይህን ስራ ለመስራት የሶስት ወር ስልጠና በቂ ሆኖ እያለ ዩኒቨርሲቲ መማር ባላስፈለ” ሲሉ የትምህርት ስርዓቱ ውድቀት እንደገጠመው መግለጻቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡
(ምንጭ: golgul  ነገረ ኢትዮጵያ ፌስቡክ – ፎቶ ከፋይል ማህደር)

ያልተገራው ገሪ …. ኢቲቪ (ጌታቸው ሺፈራው)


 
 
  •  
    Share
በጌታቸው ሺፈራው
ህወሓት/ኢህአዴግ ስልጣን ከያዘበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ደቡብ አፍሪካ ያሉ አገራት ነጻነታቸውን አግኝተው የዓለም ቀጣይ ኃያል አገራትን ተቀላቅለዋል፡፡ አብዛኛው የዓለም ማህበረሰብ ዴሞክራሲያዊ በሆኑ ስርዓቶች ለመተዳደር እድል አግኝቷል፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ ግን ስልጣን ከያዘ ማግስት በህግ ፈቀድኩት ያለውን የሚዲያ ነጻነትን ጨምሮ በማፈን፣ በዛው በርሃ ውስጥ በነበረው ‹‹ውርጋጥነቱ›› ቀጥሏል፡፡ አሁንም ቢሆን ‹‹ሲቪል›› ነኝ ብሎ የሚያስበው በአፈሙዝ ነው፡፡ በአንድ በኩል ዴሞክራትነቱን እያስወራ በተግባር ግን የአምባገነኖች ቁንጮ ሆኖ ቀጥሏል፡፡ በአጠቃላይ በርሃ ከነበረበትም በባሰ አሁንም እንዳፈተተው በኢትዮጵያውያን ላይ ስልጣኑን የሚያስጠብቅለትን እርምጃ መውሰዱን ቀጥሏል፡፡ ኢህአዴግ አልተገራም፡፡
safe_image
እንዲያም ሆኖ ግን ሌሎቹን ስለ መግራት ያወራል፡፡ ትናንትና ማታ (ነሐሴ 19/2006) በልሳኑ ያሳየው ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› የተሰኘ ፊልም የሚያሳየውም ይህንን ከአለ-አቅም መንጠራራትን ነው፡፡ ኃይሌና ገና በጋዜጠኝነት ተመረቁ የተባሉ ወጣቶች የእነ ፕሮፌሰር መስፍንን፣ የእነ ዶክተር በድሉ ዋቅጅራን፣ የእነ ተመስገን ደሳለኝን፣ የእነ ዓለማየሁ ገላጋይን ብዕር ‹‹ሊገሩ›› ሲፍጨረጨሩ ማየት በእጅጉ የሚያስገርም ነው፡፡

ሲያሸንፍም በስሜት የዘለልንለት፣ ሲሸነፍ የተሸነፍንለት የድሮው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ከስርዓቱ ጋር አብሮ ‹‹ሚዲያ ኑክሊየር ነው!›› ሲል ‹‹አጥፊነቱን›› መስክሯል፡፡ በእርግጥ ኃይሌ በህዝብ ላይ ሲቀልድ ይህ የመጀመሪያው አይደለም፡፡ ከአመት በፊት በሰይፉ ፋንታሁን የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ስለ መምህራን የደሞዝ ጭማሬ ተጠይቆ የመምህራኖቹ የደምወዝ ጭማሬ ቅብጠት መሆኑን ተናግሯል፡፡ ከአንድ አስተማማኝ የመረጃ ምንጭ እንዳገኘሁት ከሆነ ኃይሌ ገብረስላሴ ለስርዓቱ አፋኝነትም በግልጽ ድጋፉን እያሳየ እንደሚገኝ ነው፡፡ የመረጃ ምንጩ እንደጠቀሰልኝ የተቃዋሚ ፓርቲ አባላት የሚታጎሩበት የካ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ ማስፋፊያ የተሰራው በኃይሌ ገብረስላሴ የገንዘብ እገዛ ነው፡፡ ለዚህ ፖሊስ ጣቢያ ካቴና ከውጭ አገር ያስመጣውም ኃይሌ ገብረስላሴ እንደሆነ ምንጩ ገልጾልኛል፡፡
በርካታ ኢንቨስትመንቶቹ በገዥው ፓርቲ ይሁንታ እንደሚቀጥሉ ያመነ የመሰለው ኃይሌ ትናንትናውም ቢሆን የስርዓቱ መሳሪያ ሆኖ ሚዲያውን ሲተች ያመሸው ከራሱ የኢኮኖሚ ጥቅም አንጻር ነው፡፡ ኃይሌ ከኑክሊየርም በላይ አፍራሽ ነው ያለውን ሚዲያ መተቸት የጀመረው በአንድ ዘገባ ምክንያት አንድ የውሃ ፋብሪካ መዘጋቱን በመግለጽ ነው፡፡ ኃይሌ ይህን ወደ ራሱ አስጠግቶ ሲያጠናክርም ‹‹በእኔ ላይ በመጻፉ ልጆቼ፣ ቤተሰቤ ያያሉ፡፡ በስሬ 1500 ሰራተኛ አለ፡፡ አዋሳ፣ ባህርዳር፣…ያሉት ሰራተኞችም ያዩታል፡፡ ሰራተኞችም ይህ ሰው ምን ነካው ይላሉ፡፡ ቢዝነስ ‹ኮላፕስ› ያደርጋል፡፡›› ሲል ነበር የገለጸው፡፡ እንግዲህ ገና የኃይሌ ልጅ ትሰማለች ተብሎ፣ ሰራተኞቹ ‹‹ምን ነካው!›› ስለሚሉ፣ ‹‹ቢዝነሱ ኮላፕስ›› ስለሚያደርግ ኃይሌ ምንም ያህል ቢያጠፋ ሚዲያው ትንፍሽ ላይል ነው ማለት ነው፡፡ ይህን የኃይሌን ሀሳብ የጋዜጠኝነት ትምህርት ቤት ውስጥ መምህር ነች የተባለችውም ‹‹የሰዎች ጓዳ (መቼስ ሚስጥር ማለቷ ነው) ሚዲያ ላይ መውጣት የለበትም፡፡›› ስትል ሀሳባቸውን ተሰብስበው የተስማሙበት አስመስላዋለች፡፡ በቃ ሚዲያ ሚስጥር የማውጣት ሚናውን በእነ ኃይሌ ዳኝነት ተቀማ ማለት ነው፡፡ እነ ኃይሌና ዶክተር አሸብር ለስርዓቱ ክንድ በሆኑበት በዛው ፊልም ላይ ካሳ ተከፍሏቸዋል፡፡ ለዚህም ነው ‹‹ኃይሌ ገብረስላሴ ሊወዳደር ነው፣ ዶ/ር አሸብር አምባገነን ነው›› የሚሉ ዜናዎችና ትችቶች ሳይቀር በአጥፊነት የተፈረጁላቸው፡፡
ሚዲያ ከሌለው መንግስት ይልቅ መንግስት የሌለው ሚዲያ ይሻላል የሚል መርህ የሚከተሉትን የእንግሊዝና የአሜሪካን ዴሞክራሲ አውቀዋለሁ ያለው ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ሚዲያ ‹‹ያልተገራ›› በመሆኑ በሚያሳስብ መልኩ ያ ስቅስቅ ብሎ ያለቀሰለትን ጠቅላይ ሚኒስትር ‹‹ራዕይ›› እናስጠብቃለን የሚሉ አካላት እርምጃ እንዲወስዱ ፍርደ-ገምድልነቱን አሳይቷል፡፡
ስርዓቱን የማዳን እርብርብ
በዚህ ፊልም ላይ ስለ ሰራዊት ፍቅሬ የፍቅር ደብዳቤ መጻፍ፣ በሞቅታ ስለሚጨፍሩት አርቲስቶች አስተያየት መስጠት በአውዳሚነት አስፈርጇል፡፡ ይህ የሆነው እነዚህ ‹‹ልማታዊ አርቲስቶች›› ያልተገራው ስርዓቱ ቅቡልነት እንዲያገኝ ሳይታክቱ የሚሰሩ በመሆናቸው ነው፡፡ ከዚህ በተጨማሪ ‹‹አባይ ለፕሮፖጋንዳ አይዋል›› ማለት ብሄራዊ ደህንነትን ተጻርሮ የቆመ አስመስሏል፡፡ ከምንም በላይ ስርዓቱ ለስልጣኑ መሰረት አድርጎ የሚወስዳቸው አንጓዎች በሚዲያው ሊነኩ የማይገባ ‹‹ቀይ መስመሮች›› ተደርገው ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡ መቼም አንድ ተቃዋሚ መንግስትን የተቆጣጠረውን ፓርቲ ከስልጣን አውርዶ መንግስት ለመሆነ ነው የሚሰራው፡፡ ያልተገራው ‹‹መንግስት›› መሳሪያ የሆኑትና እነሱም ከስርዓቱ ጋር በጥቅም ከመጋራታቸው ውጭ የተገራ ነገር ያልታየባቸው ነገር ግን የተገሩትን ሲያጣምሙ የታዩት የፊልሙ ሰሪዎች ግን ‹‹ህዝብ ሌላ መንግስት ለማየት ፍላጎት አለው›› የሚለውን ከኑክሊየርም በላይ አጥፊ ነው ብለው ፈርጀውታል፡፡ ጋዜጠኝነት ‹‹በራዲካል ሮል›› ፖሊሲ የማስቀየር ሚና አለው ብለው ሳይጨርሱ ‹‹የብሄር ፌደራሊዝሙ እርምት ያስፈልገዋል›› የሚልን መካሪ ጽሁፍ በአሉታዊነት ለፈውታል፡፡ የ‹‹ብሄር ፖለቲካው›› ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም አይነት ያልተገራ አቋማቸውን ዳግመኛ አሳይተውበታል፡፡ ጠባብ አለመሆናቸውን ማሳመን ሲያቅታቸው ጠባብነታቸውን የሚተቹትን ሚዲያዎች ያልተገሩ ሲሉ ወርፈዋቸዋል፡፡ እነሱ አንዳንድ ተቋማት ስለ ‹‹መንግስት›› ያወጧቸውን መልካም የሚባሉ ነገሮች አመት ሙሉ እንደማይደጋግሙ ዓለም አቀፍ ተቋማት ስለ ድህነት፣ የመፈንቅለ መንግስት ስጋትና ሌሎችም ጉዳዮች ላይ ያወጧቸውን ሪፖርቶች የግል ሚዲያው እንዳያወጣ ቅድመ ክልከላ አውጀዋል፡፡ ማጎሪያ ቤት ውስጥ ያለውን ስቃይ ማስተባበል ሲያቅታቸው ‹‹ማረሚያ የሚያስፈልገው ማረሚያ ቤት›› የተሰኘን መካሪ ጽሁፍ በህገ ወጥነት ፈርጀውታል፡፡
ኢህአዴግ የውድቀት ዋዜማ፣ ኢትዮጵያ ለምን አሚሶንን ተቀላቀለች? ፍትህ በሌለበት የፍትህ ሳምንት፣ ለአክራሪነት አስተማሪው ማን ነው? ለተሰኙት መልስ መስጠት ሲያቅታቸው፣ እውነት ሆኖ እንቅልፍ ሲነሳቸው በጸረ ሽብር ህጉ አውድ አሸባሪ ብለው ፈርጀዋቸዋል፡፡ በጣም የሚገርመው አብዛኛዎቹ ጽሁፎች በጥያቄ የቀረቡና ኢህአዴግን ብቻ ሳይሆን የተለያዩ አካላትን ተጠያቂ የሚያደርጉ ሲሆኑ ኢህአዴግ ግን ቀድሞ ‹‹እኔን ነው›› ብሎ ለራሱ ወስዷቸዋል፡፡ ሚዲያው ገለልተኝነቱን እያሳየም ቢሆን እነሱ የአንድ አካል አፈ ቀላጤ ይሉታል፡፡ ለዚህ እንደ ማስረጃ ያቀረቡት ደግሞ ‹‹ማንን እንመን?›› በሚል የወጣን አንድ ጽሁፍ ነው፡፡ ይህ ጽሁፍ ዶ/ር ብርሃኑንና በረከት ስምዖንን ያፋጠጠ ጽሁፍ ነው፡፡ ከሁለቱ አካላት ማንንን እንመን ተብሎ በማነጻጸሪያነት የወጣውን ይህን ጽሁፍ ራሱን የማያምነው ኢህአዴግ ‹‹እኔን ነው የማያምኑኝ›› ብሎ ጥፋቱን ቀድሞ ወስዶ ‹‹የአንድ አካል አፈቀላጤ ሆነዋል›› ሲል ይከሳል፡፡
በአጠቃላይ ‹‹ያልተገሩ ብዕሮች›› በሚል የቀረበው ፊልም የኢህአዴግን ፖሊሲ መተቸት ህገ ወጥነት እንደሆነ የታየበት፣ የስርዓቱ ዋና ዋና የስልጣን ማቆያ ፖሊሲዎችን መንካት ስርዓቱን ሊያፈራርሰው እንደሚችል ባልተገራ አንደበት የተነገረበት ፊልም ነው፡፡ በፊልሙ ተዋናይ የሆኑት አካላት እዛው ፊልሙ ላይ ‹‹ፌቨር›› እየተሰራላቸው በትውልዱ ላይ ሲፈርዱ ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ እንደሆኑ በግልጽ ለማየት ተችሏል፡፡ ሁሉንም ነገር ከኢኮኖሚ አንጻር ሲቃኝ ያመሸው አትሌት ኃይሌ ገብረስላሴ ‹‹ጦርነት ከፈታው ወሬ የፈታው›› በሚል ኃይል በእጁ ለሆነው ያልተገራ ስርዓት በቅኔ እርምጃ እንዲወስድ አሳስቧል፡፡ የስፖርት ጋዜጦች ድረስ ተሂዶ የተደረጉበት ጥቃቅን ትችቶች በህገ ወጥነት የተፈረጁለት ዶክተር አሸብር በግልጽ አገልጋይነቱንና ስርዓቱን ለማዳን የቆመ መሆኑን አሳይቷል፡፡ ፓርላማ ላይ ኢትዮጵያ ምንም አይነት ጥቅም ሳታገኝ ለጅቡቲ ውሃ የሚለግሰውን አዋጅ ከተቃወሙት መካከል ዶክተሩ አንዱ እንደነበሩ በሚዲያ ተገልጾ የነበር ቢሆንም ዶክተሩ ግን ስለ አዋጁ ያላቸውን ይሁንታ ሲገልጹ ‹‹ከእኛ ጋር ሳይደርስ ለምን አይጸድቅም?›› የሚል ጥያቄ አቅርበው እንደነበር ገልጸዋል፡፡ የህዝብ ተወካይ ነኝ ብሎ አንድን ህግ ‹‹ፓርላማ ሳይመጣ ለምን ራሱ ኢህአዴግ አያጸድቀውም›› ማለት ስርዓቱን ለማዳን እርብርብ ላይ መሆናቸውን የሚያሳይ ነው፡፡
በአጠቃላይ በፊልሙ ላይ በአሉታዊነት የተፈረጁት ጽሁፎች ቢበዛ መካሪ ቢሆኑ እንጂ ይህ ነው የሚባል ‹‹አለመገራት›› አይታይባቸውም፡፡ ነገር ግን ባለመገራቱ ሳይነካ የሚደነብረውን ስርዓት ይበልጡን የሚያስበረግጉ መሆናቸው የሚያስገርም አይሆንም፡፡
እነ ኃይሌ ዴሞክራሲን አይቼባቸዋለሁ ባሏቸው አገራት ሚዲያ አራተኛ የመንግስት አካል ቢሆንም ኢትዮጵያ ውስጥ ሶስቱ የመንግስት አካላትም ሆነ መንግስት ባለመኖሩ አራተኛ መንግስት ሊሆን አልቻለም፡፡ ከዚህ ይልቅ መንግስት በሌለበት፣ ካልተገራ ዘመናዊ የቤተ መንግስት ወንበዴ ጋር ግብ ግብ የሚገጥም ብቸኛው የመንግስት አካል ሆኖ ለማገልገል ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል፡፡ ይህ ደግሞ መንግስትም ሆነ የመንግስት አካላት እንዳይኖሩ የሚፈልገውንና ልጥ ሲያይ እባብ ነው ብሎ የሚደነብር ያልተገራ ስርዓት እጅጉን አስደንብሮታል፡፡ ስለ ተገራና ስላልተገራ ብዕር ይህ ነው የሚባል እውቀት የሌላቸው፣ የማያገባቸው እነ ኃይሌም ያልተገራው ስርዓት ጋር የተጋሩትን ጥቅም ለማስጠበቅ ሲሉ ስርዓቱ በሚዲያው ላይ እርግጫውን በመሰንዘር እራሱን እንዲያድን እርብርብ አድርገዋል፡፡ የእነ ኃይሌ ምክር ስርዓቱ እንደለመደው እንዲራገጥ የሚገፋፋ ቢሆንም ማዳን አለማዳኑንም ሆነ እነሱ በትውልዱ ላይ እየፈጸሙት ያለውን በደል ግን ታሪክ የሚፈርደው ይሆናል፡፡

Tuesday, August 19, 2014

ሻእቢያ ከከረን እና ከአስመራ ጦሩን ወደ ተሰንይ ማስፈሩን ተከትሎ ወያኔ ተጨማሪ ጦር ሲያጓጉዝ ዋለ።

የመከላከያ ሰራዊቱ ሊከዳ ይችላል በሚል ስጋት የወያኔ ጄኔራሎች ሲመክሩ ውለዋል።

Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ከሩሲያ ጋር የጦር ልምምድ ስምምነት እንዳደረገ የሚነገርለት የኤርትራ ገዥ ቡድን ሻእቢያ ከባለፉት ወራቶች ጀምሮ ጦሩን ወደ ደቡባዊ የኤርትራ ግዛቶቹ በመሰብሰብ ላይ መሆኑን ተከትሎ ወያኔም እንዲሁ ባለፈው ካሰፈረው ሰራዊት በተጨማሪ ከትላንትና ጀምሮ ከባድ የጦር ተሽከርካሪዎችን እና ተጨማሪ የጦር ሰራዊት በአከባቢው በማስፈር ላይ መሆኑ ታውቋል።

አሜሪካ እና ሩሲያ በአከባቢው ያላቸውን የበላይነት ለመቀዳጀት ፉክክር በገቡበት በዚህ ወቅት አከባቢው የጦርነት ቀጠና እንደሚሆን ቀድማ አሜሪካ በበረራ ደህንንነ ሰበብ ሹክ ባለችበት ሰአት እንዲሁም የሻእቢያ ተቃዋሚ ሃይሎችን ወያኔ በገንዘብ እና በቅስቁስ እየረዳ ባለበት ጊዜ በተጨማሪም በአግል ወያኔያዊ ትእቢት እየዛተ እንዳለ ሲሆን ለወያኔ ከፍተኛ ስጋት የሆኑበት ኢርታራ ውስት የመሸጉ ተቃዋሚ ሃይላት ስለሆኑበት በጭቆና የተምረረው ምከልከያ ሰራዊት ተቃዋሚዎችን ይቀላቅላል የሚል ከባድ ስጋት በሕወሓት ጄኔራሎች ላይ መከሰቱን ምንጮች ጠቁመውል።

ወያኔ በቅርቡ ከዩክሬይን ያስገባችቸን ቲ-72 ዘመናዊ ታንኮች በጦርነት ላይ ለማሰለፍ ወደ ሰሜን እያጓጓዘ ሲሆን ሻእቢያ በበኩሉ ሩሲያ ሰራሽ የሆኑ ዘመናዊ ታንኮች ሚሳኤሎች እና ከባባድ መሳሪያዎች፡ጸረ አይሮፕላን መድፎችን በአከባቢው አስፍሯል። ወያኔ ዘመናዊ መሳሪያ እና በታንክ ላይ የተጠመዱ መድፎችን ቢያምጣም በመክላከያ ሰራዊቱ ላይ ምንም አይነት መተማመን እንዳሌለው እየተናገረ ሲሆን በሰሜናዊ ትግራይ ብግብርና ሙያ ላይ ከነሙሉ ትጥቃቸው ያሰፈራቸውን የቀድሞ ታጋዮች እየቀሰቀሰ መሆኑ ሲታወቅ ህዝቡ ጦርነት እንደተሰላቸ እና ባለው ስርአት ላይ እምነት እንዳጣ በግልጽ እየተናገረ መሆኑ ታውቋል።

በሰራዊቱ ያልተማመነው ወያኔ አንድ የወሰደው እርምጃ ከሱዳን ጋር ያደረገውን የሰራዊት ቅልቅል ሲሆን ይህም ተቀላቅሎ መስራት በሰራዊቱ መኮንኖች ዘንድ ተቀባይነት አለማግኘቱ ታውቋል። የምዕራብ ኢትዮጵያን መሬት ለሱዳን ለመስጠት ያሰበውን አገር የማጥፋት ሴራ ተግባራዊ ለማድረግ መሆኑን እና ሰራዊቱም ይህንን ተረድቶ ላገሩ ክብርና ታሪክ እንዲቆም ህዝቡ እየትናግረ ሲሆን የተደረገው የሰራዊት ውህደት ሱዳን በዳርፍርና ምስራቅ ሱዳን እንዲሁም ከደቡብ ሱዳን አቅጣጫ ላለበት ጦርነት በስምምነታቸው መሰረት የኢትዮጵያ ወታደሮች እንዲዋጉለት ለማድረግና ወያኔም በዚህ ጉዳይ ላይ መስማማቱን እናም በመከላከያ ሰራዊት ያለ የኢትዮጵያ ወጣት በጎረቤት አገሮች የበረሃ ሲሳይ ከመሆን ራስን እንዲታደግ አስተያየት ሰጪዎች አሳስበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ከአዲስ አበባ የሚወጡ ዘገባዎች መጭውን የወያኔ የጦርነት ዝግጅት ተከትሎ የመከላከያ ሰራዊቱ በመክዳት ከተቃዋሚ ሃይሎች ጋር ሊቀላቀል ይሽላል በሚል ስጋት ስብሰባ ተቀምጠው መዋላችውን ምንጮች ጠቁመዋል። በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የተቃዋሚ ሃይሎች የሚያወጡት መግለጫ በሰራዊቱ ላይ የሚፈጸመው ዘረኝነት እንዲሁም ብዝበዛ እና ከሃገሪቱ ጥቅሞች አንጻር እየተደረገ ያለው ብሄራዊ ውርድት በእጅጉ አሳሳቢ ደረጅ ልይ መድረሱ ሕዝቡ ለስር አቱ ያለው ጥላቻ መበራከቱ እንዲሁም ከዚህ ቀደም በባድመ ጉዳይ የተፈጸሙ መንግስታዊ ማጭበርበሮች እና የመሳሰሉት ግኡዳዮች ሰራዊቱ ይከዳል የሚል ከባድ ስጋት ያላቸው መሆኑን ያወሱት ጄኔራሎቹ በመከላከያ ሰራዊቱ ላይ እምነት በማጣትቸው ትግራይ ያለው የሕወሓት ታጣቂ ሃይል ከጀርባ እንደ ደጀን እንደ መተማመኛ እንደሚወስዱት መክረዋል።

ሰራዊቱ ያለውን ስርአት በተመለከት ደስተኛ ስላልሆነ እንዲሁም ሕዝቡ የሚፈልገው ለውጥ እንጂ ጦርንት ስላልሆነ ወያኔ በመጭው ሊያደርገው ያሰበው ጦርነት ከባድ ኪሳራ ያስክትልበታል ተብሎ ተገም

ለራሱ ነፃነት የሌለው ድረጀት የህዝቦችን ሰበአዊ እና ዴሞክራሲያዊ መበት ተግባርዊ አያደርግም ! የመኢአድ ሰሞነኛ ውዝግቡ !

 መኢአድ በመጣባቸው አስቸጋሪ የትግል ጊዜያት አሁን ላይ እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡ ታህሣስ 15- 17, 2003 ዓ. ም ወዲህ በአመራሩ ላይ በደረሰ ክፍፍል ፓርቲው ይህ ነው የሚባል ስራ ለመስራት እየተውተለተለ እስከ ነሐሴ 11 ቀን 2006 ዓ. ም ደርሶ በመካከሉ ይፈታል የተባለው የእርቅ ሂደት መና ሊቀር ችሏል፡፡

ጉዳዩ በፍ/ ቤትና በምርጫ ቦርድ ተይዞ መጠራቅቅ ውስጥ የወደቀው የፓርቲው ሕልውና የውስጥ ችግሩን ፈትቶ ከአንድነትና ከሌሎች ፓርቲዎች ጋር ተዋህዶ አንድ ወጥ ሀገራዊ  ችግር ይፈታል ተብሎ ሲታሰብ ‹‹ሽማግሌ›› ተብለው በተመረጡት በነ ዶ/ር በዛብህ ዝርክርክነት ያለውጤት በቁርሾ እንዲበተን ተደርጓል፡፡

ለአለመግባባቱ ምክንያት አቶ አበባው መሀሪ፣ ወያኔ አስርጎ ካስገባቸው፡- ሙላጌታ አበበ÷ ተስፋሁን አለሙ÷ መላኩ…እና ከትግራይ በወያኔ ተልከው ከመጡ መሰሉና ጋዳፊ በተባሉ‹ባልና ሚስት›(እነዚህ ቀደም ሲል በመኢአድ ውስጥ የትግራይ ተወካይ ነን በማለት መኖሪያ ቤታቸውን ቢሮ ነው በሚል ኪራይ ሲቀበሉና በጀት ተመድቦላቸው ሲያምታቱ የነበረ÷ ከ2004 ዓ. ም በኋላ አንድነት ፓርቲ ገብተው 4.000.00ብር በመቀበል አንዷለም አራጌን በመሰለል ለእስር ከአበቁ በኋላ ራእይ ፓርቲ ገብተው ሲያንጎዳጉዱ የነበረ÷ አሁን ከአቶ አበባው ጋር በመኢአድ የሚያነኩሩ ዋና ተሰላፊ ናቸው) ÷…ትክክለኛ አባላቱ ገብተው በተመረጡ ‹ሽማግሌዎች› አማካኝነት የተከሰተው ችግር በጭዋነት ተወያይተው ይፈታል ተብሎ በመታመኑ፡- ወ/ሮ ሳባ መኮንን የመአሕድ/መኢአድ መስራችና ታጋይ በቦታው በመገኘት፣ በምርጫ ግርግር ልጃቸው የሞተባቸው ወ/ሮ ይታይሽ አያሌው ድፎ ዳቦ ይዘው በመምጣት፣ ታህሣስ 17 ቀን 2003 ዓ. ም በጠቅላላ ጉባኤው ወቅት የኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ በኢ/ር ሀይሉ ጉልበት ላይ በማስቀመጥ የተፈጠረው ችግር ሳይፈታ የት ነው የሚሄዱት ያሉት(ዛሬ ላይ ሞቸ በነበር ብለው የሚፀፀቱ) አቶ ነብዩ ዓለምይሁን ከስምምነቱ በኋላ ሁሉም አባላት የሚደርስ ጧፍና ሻማ ይዘው በመምጣት፣….ሌሎችም ነባር አባላት ተገኝተው እያለ ነው ከላይ በተጠቀሱት ‹አመራር › ተብየዎች ሊከሽፍ የቻለው፡፡ በእለቱ ቁጥሩ የበዛ ‹ደህንነት›፣ ፖሊስ፣ ኢዜ..አ….በጽ/ ቤቱ ዙሪያ ከበው ጉዳዩን ሲከታተሉ ነበር፡፡
መኢአድ ለአለፉት 3ዓመት ከ8 ወር ከ5 ቀን ወይምለ1349 ቀናት ከ18 ስዓትት ወይም ለ80,445 ሠዓታት ከማባከኑም በላይ ፤ የምዕራብ በለሳ የ2002 የተወካዮች ም/ ቤት ዕጩ አቶ ምሳው ዮሐንስን ጨምሮ ከማእከል 4 አባላቱን በወያኔ ገዳዮች በማስገደል፣ አቶ ብርሀኑ አባሆይን በመጥረቢያ ወገቡን በማስመታት፣….ቁጥሩ የበዛ አመራሩና አባላቱን በማሳሰርና በማስደብደብ፣…ለዘርፈ ብዙ ችግር የተጋለጠ፣ 2 በኢየሩሳሌም ሆቴልና በዋናው ጽ/ ቤቱ ያልተገባ ጠቅላላ ጉባኤ‹አድርጌአለሁ› ብሎ ብዙ ገንዘብ ያባከነ፣ በጽ/ ቤቱ ውስጥ ላሉት የወያኔ ደህንነቶች ወርሀዊ ደሞዝና አበል የሚከፍል፣ የበርካታ አባላቱንና የህዝቡን ምስጢር ለወያኔ እያሰጠ በራሱ ላይ ችግር የሚያደርስ(ገዥው ፓርቲ የተቃዋሚዎች እንቅስቃሴ 99% በእጃችን ነው ይላል)፣…..እቶ ያእቆብ ልኬ፣ አሰፋ ሀ/ ወልድ፣ አበባው መሀሪ፣….የተባሉ ፎርጅድ ‹መሪዎችን› በኢ/ር ሀይሉ ፈቃጅነት ባልተሟል ጉባኤ መርጫለሁ ብሎ እየዳከረ፣ ….የሚገኝ ፓርቲ ነው፡፡
ይሁንና በጠናካራ አባላቱ፣ አመራሩ፣ ደጋፊውና፣…..በሚቻለው መጠን ወደነበረበት ለማስመለስ ጥረትና ተጋድሎ እየተካሄደ ነው፡፡
አንድ ሊገነዘቡት የሚገባ አብይ ነገር ግን ለሚባክነው፡- ጊዜ፣ ጉልበት፣ የሰውኃይል፣ ገንዘብ፣ ውድ የቅስቀሳ ሥራዎች፣ በአባላቱና በአመራሩ ለደረሱትና ለሚደርሱት ማናቸውም ነገሮች፣…..ሁሉ አቶ አበባው(ኢ/ር ሀይሉ)እና በስራቸው ያሉት ወያኔዎች የሚያወራርዱት መሆኑን እንዲያውቁት የእምየ ኢትዮጵያ ቁርጥ ልጆች አበክረው ያሳስባሉ!!! በሕይወት፣ በደም፣ በሀገርና በሕዝብ፣ በገንዘብና በጊዜ ላይ የሚቀልዱት፣…. ሁሉ ‹‹ዝም›› ተብሎ የሚታለፍ አይደለም!!!
ርእየ- ሁለንተና             « ታምራት ይደጎ »
13/ 12/ 2006 ዓ. ም
አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ

Friday, August 1, 2014

አቶ በረከት ከሆስፒታል ወጥተው ወደ አልታወቀ ስፈራ መወሰዳቸው ተገለፀ

ሰሞኑንን ጅዳ ሳውዲ አረቢያ አንድ ሪፈራል ሆስፒታል በህክምና ላይ የነበሩት አቶ በረከት ስሞኦን ሞቱ እይተባለ የሚናፈሰው ዜና ትክለኛ አለመሆኑን የሚገልጹት ምጮች ። የመንግስት ባለስልጣኑ ዛሬ ማምሻውን ከሆስፒታል ወጥተው ሼክ አላሙዲን ወደ አዘጋጁላቸው ሆቴል «ማረፊያ» ማቅናታቸውን አረጋግጠዋል። 
እሁድ ለሊት በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን ሳውዲ አረቢያ ለህክምና በሚስጠር የገቡት እኚሕ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የልባቸውን የደም ቧንቧ ለማስፋት የተደረገው ህክምና ስኬታማ እና ለክፉ ችግር የማይሰጣቸው መሆኑን የሆስፒታሉ ምንጮች ቢገልጹም የባለስልጣኑ የሰውነት አቋም ከትጎሳቀለው እና ከወትሮው ለየት ባለ መልኩ የጠቆረው ፊታቸው ገጽታ ሰውነታቸው ውስጥ መልካም ነገር እንደሌለ ያመላክት እንደነበር በአካል ያዮቸው የአይን እማኞች አቶ በረከት በቀርብ ቀን ወደ ሃገር ቤት አሊያም ለተሻለ ህክምና ወደ አውሮፓ ለማቅናት እቀድ እንዳላቸው ገልጸዋል። ዛሬ ረፋዱ ላይ አቶ በረከት ከሚያገግሙበት ሆስፒታል ለቀው ከመውጣታቸው ቀደም ብሎ ለጉብኘት ወደ ሆስፒታሉ አቅንተው የነበሩ ምንጮች በአካባቢው ምንም አይነት እንቅስቃሴ እንዳልነበረ እና ኢትዮጵያውያን ሳይሆኑ እንዳልቀሩ የሚገመቱ ነጭ ለባሾች ሆስፒታሉ አካባቢ መታየታቸውን አረጋግጠዋል፡፤ 
ይህ በዚህ እንዳለ ከአቶ በረከት ስሞኦን ጋር የመጡት የጦር ሃይሎች ሆስፒታል ዶ/ር ወደ ኢትዮጵያ ለመመለስ በዝግጀት ላይ መሆናቸውን እነዚሁ ምንጮች አክለው ገልጸዋል። ። የአቶ በረከት ስሞኦን የጤንነት ሁኔታ በተመለከት ከጅዳው የኢትዮጵያ ቆንሳል ጽ/ቤት መረጃ ለማግኘት ያድረኩት ሙከራ ባይሳካም ለዕረፍት ሀገርቤት የሄዱትን ቆንስላ ሸሪፈን ተከተው ወ/ሮ ሙንተሃ ወደተጠቀሰው ሆስፒታል ሰው እየላኩ የኚህን ባለስልጣን የጤነነት ሁኔታ በቀርብ በመከታተል ላይ መሆናቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል። 
ባለስልጣኑ የሚገኙበትን የጤና ሁኔታ ካረፉበት ሁቴል የምናገኘውኝ መረጃ እይተከታተለን ለማቅረብ ይሞከራል Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ

Wednesday, July 30, 2014

«አሳዛኝ ዜና »ህክምና ላይ የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን በህይወት የመቆየት እድላቸው አስተማማኝ እንዳለሆነ የሆስፒታሉ ሚስጥራዊ ምንጮች ገለጹ

 ሰሞኑን ሳውዲ አረቢያ  ጅዳ ከተማ አንድ ሆስፒታል  «ቡግሻን» hospital ተኝተው  የሚገኙት አቶ በረከት ስሞኦን የህክምና ግዜያቸውን  ሳይጨርሱ ከሆስፒታሉ እንዳይርቁ ዶክተሮቹ አስጠነቀቁ ፡፤  የመንግስት ባለስልጣኑ ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን የግል አይሮፕላን ሲያቀኑ በሁለት እና በሶስት ቀናት የተጠቀሰውን ህክምና በአጭር ግዜ ውስጥ አጠናቀው  እንደሚመለሱ ተስፋ ቢያደርጉም ቀደም ብሎ ደቡብ አፍሪካ ላይ የተደረገላቸው የልብ  ህክምና ባለስልጣኑን ለከፋ አደጋ ሳይዳርጋቸው እንዳልቀረ የሚገልጹት የሆስፒታሉ የምርመራ ምንጮች  አቶ በረከት ስምኦን ዕረፍት ካልወሰዱ እና የዶክተሮች ቀርብ ክትትል ካልተደረገላቸው በህይወት ሊቆዩ እንደማይችሉ አስታውቀዋል።
አቶ በረከት በአሁኑ ሰአት በተጠቀሰው ሆስፒታል ውስጥ የእግር እንቅስቃሴ እንዲያደርጉ ዶክተሮች እንዳዘዟቸው እና የሆስፒታሉ አርማ ያረፈበት  የማታልብስ «ቢጃማ» መስል ነገር ለብሰው  4 ፎቅ ሲዊት ሩም 501 በረዳ ላይ ከአንድ ረዘም ካለ ደንዳን ሰውነት ካለው ሰው ጋር ሲጓራደዱ መታየታቸውን የአየን እማኞች አረጋግጠዋል። አቶ በረከትን ለማረጋጋት አላሙዲን በስልክ እና በአካል ከሚያደርጉላቸው ማጽናናት ውጭ እስካሁን ሄዶ ያያቸው ዲፕሎማተም ሆነ የመንግስት ባለስልጣን እንደሌለ እየተነገረ እንዚህ እማኞች ገልጸዋል። 
ይህ በዚህ እንዳለ አቶ በረከትን አልፎ አልፎ ወሰድ « ፌንት »  የሚያደርጋቸው ነገር የልብ ምት አለመስተካከል መሆኑን በድፍረት መናገር ቢቻለም  የኚህን የመነግስት ባለ ስልጣን እድሜ መገመት አግባብ እንዳልሆነ የገለጹ አንድ ስለ አቶ በረከት ጤንነት በቀርብ የሚከታተሉ ዶክተር ለታካሚውም ሆነ ለቤተሰቦቹ ታካሚው ይሞታል  ብሎ መናገር ሙያዊ ስነምግባር እንዳልሆነ ተናግረው ታካሚው የልብ ምታቸው ተሰተካ ክሎ ከዚህ ሆስፒታል በሰላም መውጣት ከቻሉ ቀሪው የፈጣሪ ነው ብለዋል። እንደሚታወቀው እኚሁ ሚኒስቲር የዶክተሮችን የሰጧቸውን መረጃ አብነት በማድረግ   የቀድሞው የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር የጤነንት ጉዳይን አስመልከተው በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ጠቅላይ ሚንስትር መለሰ ዜናዊ   የጤንነታቸው ሁኔታ ተስተካክሎ በቀርብ ግዜ ወደ ነበሩበት መደበኛ ስራ እንደሚመለሱ ለኢትዮጵያ ህዝብ በገለጹ ማገስት ጠቅላይ ሚንስትሩ ከዚህ አለም በሞት መለየታቸው  የሚታወስ ነው ። Meles Zenawi is not dead, says Bereket Simon 
በአሁኑ ሰአት የመግስት ባለስልጣኑ መረጋጋት እንደማይታይባቸው እና አልፎ አልፎ እንደ  እንቀልፍ ቢጤ ጭልጥ አድርጎ የሚወስዳቸው ነገር ከልብ ምት አለመስተካከል ጋር የተያያዘ የሚፈጠር አደገኛ ነገር መሆኑን የተለያየ ሙያዊ ግምታቸውን  የሚሰጡ  የአካባቢው ታዛቢዎች በእንደዚህ አይነት መልኩ ወደ ሆስፒታሉ ለህክምና ከገቡ  ሃብታሞች እና ታዋቂ ሰዎች በሰላም ህይወታቸው ተርፎ  የወጡ ጥቂቶች ብቻ በመሆናቸው የአቶ በረከት ህይወተም ከጥቂቶቹ አንድ ይሆን ዘንድ እያለቀሱ  ሃዘናቸውን  ገልጸዋል። 
ይህ መረጃ እስከተጠናክረበት ግዜ ድረስ አቶ በረከት ስሞኦን በህይወት መኖራቸውን ያረጋገጡለን የአይን እማኞች የኢትዮጵያ መንግስት ሎኡካን ቡድን  ሰሞኑን ለጉብኘት በይፋ ወደ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ እንደሚመጣ እና የአቶ በረከት ስሞኦን የጤንነት ሁኔታ አስተማማኝ ካለሆነ መንግስት ቅድመ ዝግጅቶችን ማድረግ እንዲያስችለው ለኢትዮጵትያ ህዝብ በይፋ ሊገለጽ  እንደሚችል ከኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መ/ቤት ያገኙትን ምስጢራዊ መረጃዎቻቸውን አድረስውናል ። Ethiopia - Information Minister, Bereket Simon Press conference on the death of Meles Zenawi 


ማሳሰቢያ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ስለኚህ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ ለመረዳት የሚፈልግ ወገን ለትክክለኛ መረጃ እንደ  አመቺነቱ የሆስፒታሉን ስልክ ቁጠር ከወዲሁ ለመግለጽ ይሞከል።                             ምንጭ ታምራት ይደጎ 

Sunday, July 27, 2014

ሰበር ዜና የአቶ በረከት ስምኦን የጤንነት ሁኔታ አስጊ ደረጃ ላይ መድረሱን የሆስፒታል ምንጮች ገለጹ።

                    
 ሳውዲ አረቢያ ጅዳ ከተማ ለህክምና የገቡት እኚህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን በተለምዶ   ብግሻን የሚባል አንድ ትልቅ ሆስፒታል  4 ፎቅ የልብ ቀዶ ጥገና በተሰካ ሁኔታ እንደተደረገላቸው የሚናገሩ ውስጥ፡ አውቂ ምንጮች ከቀዶ ጥገና ክፍሉ ከወጡ በሃላ የባለስልጣኑ የጤንነት ሁኔታ ወደ ነበረበት ሊመለስ ባለመቻሉ ወደሌላ ክፍል ተዘዋውረው የቀርብ ክትትል   እየተደረገላቸው መሆኑን ለማወቅ ተችሏል። ይህ በንዲህ እንዳለ አቶ በረከት ስምኦን  ወደተኙበት ክፍል ዶክተሮች ባልተለመደ ሁኔታ እየተቻኳሉ ሲገቡ እና ሲወጡ ያዩ  የአይን እማኞች የባለስልጣኑንን በህይወት መትረፍ  ይጠራጠራሉ።
ከአንድ ቀን በፌት እዚህ ጅዳ ሳውዲ አረቢያ በሼክ አላሙዲን ማካኝነት አንድ ኢትዮጵያዊ ዶክተር አስከትለው   ለህክምና እንደገቡ የሚነገረው አቶ በረከት ስምኦን እስካሁን ስላሉበት ሁኔታ በትክከል  መናገር ባይቻለም   አብረዋቸው ከመጡት የቀርብ ቤተሰቦቻቸው ውስጥ ሚስታቸው እና ሴት ልጃቸው ሆስፒታል ውስጥ ነጠላቸውን ወገባቸው ላይ አስረው ሲላቀሱ ያዩ ታዛቢዎች  የባለስልጣኑን  በህይወት መኖር ጥያቄ ምልክት ውስጥ እንደከተተው ይነገራል።  ለአቶ በረከት አርቴፊሻል የፕላስቲክ ቧንቧ ከልባቸውጋር በድጋፍ የተገጠመ መሆኑን የሚገልጹት የሆስፒታሉ ምንጮችየባለስልጣኑን የልብ መት የሚለካ ግስቲር በተጓዳኝ መገጠሙን  እና የልብ ቀዶ ጥገናው በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን  ያረጋግጣሉ።
አቶ በረከት ስሞኦን ቀደም በልው ድቡብ አፍሪካ ውስጥ ተመሳሳይ የሆነ የልብ ቀዶ ጥገና ተደርጎላቸው እንደነበር የሚያሳዩ መረጃዎች ምናልባት በልብ ቀዶ ህክምናው ወቅት ስህተቶች ተፈጥረው በመንግስት ባላስልጣኑ ላይ አደገኛ ኢንፌክሸን ሳይፈጠር እናዳልቀር ይነገራል። አቶ በረከት ስሞን አሁን ስላሉበት የጤንነት ሁኔታ የኢትዮጵያ መንግስት ምንም ያለው ነገር ባይኖረም ስለእህ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣን የጤንነት ሁኔታ ተጨማሪ መረጃ ለመስብሰብ በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት  የሚገኙ አንዳንድ ዲፕሎማቶችን ለማነጋገር ያደረኩት ሙከራ እስካሁን አልተሳካም ።   ምንጭ   ታምራት ይደጎ  

Wednesday, July 9, 2014

አንበሳውን በጅቦች ተከቦ አየሁት ( በፋሲል የኔአለም )


ኢቲቪ የአንዳርጋቸው ንግግር ነው ብሎ ያቀረበው ፊልም አስቂኝ ነው። እንደነ ቢቢሲ በኮርፖሬሽን ደረጃ ለመዋቀር በቃሁ የሚለው ድርጅት በሴኩርቲ ( በድብቅ )ካሜራ የተቀረጸ የደበዘዘና የተቆራረጠ ፊልም ሲያቀርብ ማፈር ነበረበት።
አንዳርጋቸው ከተያዘ 2 ሳምንታት አለፉ። ዛሬ በድብቅ ካሜራ ተቀርጾ የተላለፈው ፊልም በእለቱ ኢትዮጰያ ሲገባ የተቀረጸ ነው – አለማቀፍ ግፊት ቢበዛብን እናሳየዋለን ብለው ቀርጸው ያስቀመጡት ነው። ከዚያን ጊዜ ጀምሮ ግን አንዳርጋቸው እያንዳንዷን ቀን በድብደባ እያሳለፈ ነው። ኢቲቪ ልብ ካለው አንዳርጋቸውን ላይቭ ያሳየን።
አንበሳው ለፕሮፓጋንዳ ፍጆታ የሚውል አንድም ነገር አልሰጣቸውም። “እኔ ስራየን ጨርሼ ደክሞኛል፣ እረፍት እፈለግ ነበር” ነው ያለው፤ ይህንን ደግሞ ዶ/ር ብርሃኑ ና ንቅናቄው አስቀድመው ተናግረውታል- አንዳርጋቸው ስራውን በጊዜ አጠናቆና ሃላፊነቱን ለወጣት አመራሮች ሰጥቶ እሱ መጠነኛ የዲፕሎማሲ ስራ እየሰራ ነበር።
ህወሃቶች በደንፎ “የትግራይን ህዝብ ትጠላለህ?” ብለው ጠየቁት። “ለማንም ህዝብ ጥላቻ የለኝም” ብሎ መለሰላቸው። አንዳርጋቸው የትግራይን ህዝብ ከጉጅሌው እንለየው የሚል ጽኑ አቋም ነበረው፣ያንን ነው የደገመው።
የታዩትን ፎቶግራፎች ድሮም አውቃቸዋለሁ፤ ከላፕቶፑ የተወሰዱ ናቸው። በእዚህ እድሜው የአውሮፓ ህይወቱን ትቶ በዛ አይነት ህይወት ለመኖር መፍቀዱ የሚደነቅ ነው። የእኔንም ኮምፒዩተር በቫየረስ በከሉት እንጅ እነዚህና ሌሎች ፎቶዎችም ነበሩኝ።
ፈገግታና ደግነት ደግሞ ባህሪው ነው። ጠላቶቹን ሳይቀር በፈገግታው ይገላቸዋል።
ከሁለት ሳምንት ድብደባ በሁዋላ ለፕሮፓጋንዳ የሚሆን ነገር አለማግኘታቸው ሃረር ውስጥ በጅቦች ተከቦ አልበላም ብሎ ሲታገል የነበረውን አንበሳ አስታወሰኝ።
ኮራሁብህ ወንድሜ አንዲ።

Tuesday, July 1, 2014

የግንቦት 7 ዋና ጸሐፊ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን ታገቱ ( ለኢህአዴግ ተላልፈው ከተሰጡ ድርጅቱ የበቀል እርምጃ እንደሚወስድ አስታወቀ )

የመግለጫው ሙሉ ቃል ከዚህ እንደሚከተለው ይነበባል፡፡
___________________________________________________
አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ በየመን ባለሥልጣናት እገታ ላይ መሆኑን በማስመልከት የወጣ መግለጫ

ሰኔ 23 ቀን 2006 ዓ.ም

የግንቦት 7፣ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ሰኔ 16 ቀን 2006 ዓም ለሥራ ጉዳይ በየመኒያ አየር መንገድ አይሮፕላን ተጉዞ በትራንዚት ሰንዓ ከተማ እያለ በየመን መንግሥት ፀጥታ ኃይሎች በሕገወጥ መንገድ ታግቷል። አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ የመን የጉዞው መዳረሻ አልነበረም፤ ከየመን ጋርም የሚያገናኘው ምንም ጉዳይ አልነበረውም። የየመን መንግሥት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን አግቶ ለአንድ ሰዓት እንኳን ለማቆየት ምንም ምክንያት የለውም። በዚህም ምክንያት ያለአግባብ የታገተብን የንቅናቄያችንን አመራር በአስቸኳይ እንዲፈታ በተለያዩ መንገዶች ላለፈው አንድ ሣምንት ያደረግነው ጥረት እስካሁን አልተሳካም። እንዲያውም የየመን ባለስልጣናት አምባገኑን ወያኔ ለመርዳት ባለው ፍላጎት ሳቢያ መሪያችንን አሳልፎ ሊሰጠው ይችላል የሚል ከፍተኛ ስጋት አድሮብናል።

አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ፣ በሀገራችን በኢትዮጵያ ውስጥ ፍትህ፣ ነፃነትና ዲሞክራሲ እንዲሰፍን ጊዜውን፣ እውቀቱንና ጉልበቱን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን አሳልፎ ለመስጠት የተዘጋጀ፤ ዝግጁነቱንም በተግባር ያሳየ የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። የየመን መንግሥት ከዘረኛውና ፋሽስታዊው ወያኔ ጋር በመተባበር በኢትዮጵያ የፍትህ፣ የነፃነትና የዲሞክራሲ ታጋይ መሪያችን ላይ እየፀመ ያለውን ደባ የጉዳዩ ባለቤት የሆነው የኢትዮጵያ ሕዝብ እንዲያውቅ የንቅናቄዓችን ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ወስኗል።

ትግላችን መስዋትነት እንደሚያስከፍል እናውቃለን። ከዚህ በፊትም ብዙ ጓዶቻችን መስዋዕትነት ከፍለዋል፤ ወደፊትም ብዙ መስዋዕትነት መከፈሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። አሁን በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የደረሰውና ወደፊትም ሊደርስ የሚችለው ጉዳት ምሬታችን በማብዛት፣ ቁጣችንና ዝግጁነታችን ከማጠንከር በስተቀር ቅንጣት ታክል እንኳን ወደ ኋላ እንድናፈገፍግ እንደማያደርገን ለመላው የኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለአባሎቻችንና ለደጋፊዎቻችን ሁሉ መግለጽ እንወዳለን።

መንግሥታት ይመጣሉ፣ ይሄዳሉ። ኢትዮጵያና የመን ግን ጎረቤታሞች ሆነው መቆየታቸው የማይቀር ነው። የየመን መንግሥት የወያኔ እድሜ አጭር መሆኑ የተገነዘበ አይመስልም። በዚህም ምክንያት የየመን መንግሥት የሁለቱን አገሮች ሕዝቦች የቆየ ወዳጅነት የሚያደፈርስ እርምጃ ወስዷል። የየመን መንግሥት የየመንን የወደፊት የረዥም ጊዜ ጥቅም እንዲያሰላና ያገተብንን መሪ በአስቸኳይ እንዲፈታ እንመክራለን። ይህ ሳይሆን ቀርቶ በመሪያችን ላይ ጉዳት ቢደርስ ወይም ለወያኔ አሳልፎ ቢሰጥ የመን ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር የማይሽር ቂም ውስጥ የምትገባ መሆኑን የየመን መንግሥት አውቆ በጥብቅ እንዲያስብበት እናስጠነቅቃለን።

በየመን መንግሥት አልሰማ ባይነት አቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ለፋሽስቱ የወያኔ አገዛዝ ተላልፎ ቢሰጥ በአካሉና በሕይወቱ ለሚደርሰው ሁሉ የወያኔ ፋሽስቶችን ዋጋ የሚያስከፍል መሆኑ ከአሁኑ እናስጠነቅቃለን። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስና ሕይወት ላይ የሚደርሰው ማንኛውም ጥቃት ለነፃነታቸው ለመሰዋት ዝግጁ የሚሆኑ እልፍ አዕላፍ ታጋዮችን እንደሚፈጥር ጥርጥር የለንም። በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ አካል፣ መንፈስ እና ሕይወት ላይ ለሚደርሰው ጥቃት ሁሉ በማንኛውም መንገድ በማንኛውም ቦታ የምንበቀል መሆኑንና ብዙ የወያኔ ሹማምንት ዋጋ የሚከፍሉበት እንደሚሆን እንዲያውቁት እናስጠነቅቃለን ።

በመስዋዕትነት ድልን እንቀዳጃለን።


ድል ለኢትዮጵያ ሕዝብ!!!

በርካታ የኮንዶሚኒየም ተመዝጋቢዎች ንግድ ባንክ ከምዝገባ ውጪ ሊያደርገን ነው አሉ


ተጻፈ በ ታምሩ ጽጌ
‹‹በመቆጠቢያ ደብተራችን ትክክል የሆነው ስማችን በኮምፒውተር ስህተት ነው ተባለ››  ተመዝጋቢዎች
‹‹መቆጠቢያ ደብተር ላይ ብቻ ተመዝግቦ መገኘት ትክክል ነኝ አያስብልም›› የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
በአዲስ አበባ ከተማ ከሁለት ዓመት በላይ የኖሩና ነባር ነዋሪዎች፣ የእነሱ ስህተት ባልሆነ ምክንያት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከኮንዶሚኒየም ቤት ምዝገባ ውጪ ሊያደርጋቸው መሆኑን ተናገሩ፡፡
መመዝገብና መቆጠቢያ ደብተር ይዞ መገኘት የመመዝገቢያ መሥፈርትን ማሟላት እንዳልሆነ የሚገልጸው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፣ የሚያቀርቡት መረጃ ትክክል መሆኑ ከተረጋገጠና መረጃ ሲመዘገብ የተሳሳተ ከሆነ እንደሚስተካከል አስታውቋል፡፡
በተለይ የ20/80 አዲስ ተመዝጋቢዎች በየሚኖሩበት ክፍለ ከተማና ወረዳ በአግባቡ የምዝገባ መሥፈርቶችን ካሟሉ በኋላ የቁጠባ ደብተር መውሰዳቸውን ለሪፖርተር ገልጸው፣ አንዳንዶቹ የተወሰነ ጊዜ ከቆጠቡ በኋላና አንዳንዶቹ ደግሞ ገና ምንም ሳይቆጥቡ፣ በኮምፒውተር ላይ የተመዘገበው ስማችሁና በመቆጠቢያ ደብተሩ ላይ ያለው ስም ሙሉ በሙሉ አይመሳሰልም፡፡ የተወሰኑት ደግሞ ከራሳቸው፣ ከአባታቸው ወይም ከአያታቸው ስም ላይ አንድና ሁለት ፊደላት መጉደሉ እየተነገራቸው ‹‹መቆጠብ አትችሉም›› መባላቸውን አሳውቀዋል፡፡ 
ተመዝጋቢዎቹ በተለይ የተወሰነ ጊዜ ሲቆጥቡ የከረሙት ‹‹ይኼንን ያህል ጊዜ ከቆጠብኩ በኋላ ለምን እንደዚህ ያለ ጥያቄ ታነሳላችሁ? መጀመሪያውኑ ለምን አልነገራችሁንም?›› የሚል ጥያቄ ሲያነሱ፣ ምንም ምላሽ የሚሰጣቸው ማጣታቸውን የሚገልጹት ተመዝጋቢዎቹ፣ መጀመሪያ ወደተመዘገቡበት ቀበሌ በመሄድ ከባህር መዝገብ ጀምሮ በሙሉ የሞሏቸውን ቅጾች ሲመለከቱ ሁሉም ትክክል መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ 
ትክክለኛ ማስረጃ በመያዝ ወደ ባንክ ባለሙያዎቹ ሲቀርቡ ‹‹ችግሩ የአንድና የሁለት ሰው ሳይሆን የበርካቶች ስለሆነ፣ ጉዳዩ ለባንኩ ፕሬዚዳንት ተነግሯቸው ልዩ ኮሚቴ ተቋቁሞ እየተሠራ በመሆኑ ተረጋግታችሁ ጠብቁ፤›› የሚል ምላሽ እንደተነገራቸው አክለዋል፡፡
መንግሥት የመጀመሪያውን የኮንዶሚኒየም ምዝገባ ባካሄደበት ወቀት አጥተውት ሲቆጩ ከርመው ያገኙትን የምዝገባ ዕድል፣ በእነሱ ስህተት ሳይሆን በባንኩ ሠራተኞች ስህተት እንዳያጡት ሥጋት እንዳደረባቸው የሚናገሩት ተመዝጋቢዎቹ፣ የሚመለከተው አካል ጉዳዩን ተከታትሎ መፍትሔ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ 
ተመዝጋቢዎቹ የሚያነሱትን ሥጋትና ተሳስቷል ስለሚሉት የምዝገባ ሁኔታ ለሪፖርተር ማብራሪያ የሰጡት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሙኒዩኒኬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ እንደገለጹት፣ መመዝገብና መቆጠቢያ ደብተር ይዞ መገኘት የመመዝገቢያ መሥፈርትን ማሟላት አይደለም፡፡ ቢያንስ በመንግሥት እንዲቆጠብ የተነገረውን የመጨረሻውን የቁጠባ ሒሳብ መቆጠብ እንደሚያስፈልግ ገልጸው፣ ተመዝጋቢዎች ለመመዝገብ የሚያበቋቸውን መሥፈርቶች አሟልተው ስህተት የተፈጠረባቸው በባንኩ ከሆነ ተጣርቶ እንደሚስተካከል ተናግረዋል፡፡
ለምዝገባ ፕሮግራሞቹ በተሰጠው ቀነ ገደብ ከአንድ ሚሊዮን በላይ ተመዝጋቢዎች መመዝገባቸውን የገለጹት አቶ ኤፍሬም፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመመዝገባቸው አንፃር ከ99 በመቶ በላይ በአግባቡ የተመዘገቡ መሆናቸውንና የተለያዩ ችግሮች አጋጥመዋል ቢባልም እጅግ በጣም ትንሽ መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡
ለባንኩ የተለያዩ ችግሮች መቅረባቸውን ያልካዱት ሥራ አስኪያጁ፣ ተመዝጋቢዎቹ ከተመዘገቡ በኋላ ስማቸውን በፍርድ ቤት አስቀይረው በመምጣት እንዲስተካከልላቸው የሚጠይቁ አካሄዳቸው ሕጋዊ ቢሆንም፣ በባንኩ ላይ ጫና ማሳደሩ እንዳልቀረ ተናግረዋል፡፡ መቆጠቢያ ደብተር የሚጥሉና አካውንት ቁጥራቸውን የማያውቁ እንዳሉ፣ በአስተዳደሩ በኩል ሁሉንም ቅጾች በአግባቡ ከሞሉ በኋላ በመቆጠቢያ ደብተራቸው ላይ የማይመሳሰል ስም አስመዝግበው የሚቀርቡ መኖራቸውንም አስታውቀዋል፡፡ ሌላው የተመዝጋቢዎች ስህተት በውክልና ያስመዘገቡትን ሰው ስም ይተውና በመቆጠቢያ ደብተሩ ላይ የራሳቸውን ስም አስመዝግበው የሚቀርቡ እንዳሉ፣ የራሳቸው ስም ትክክል ከሆነ የአባት ወይም አያት ስም ሙሉ በሙሉ ስህተት ሆኖ የተመዘገቡ እንደሚያጋጥሙና በመጨረሻ ተመዝጋቢዎቹ የተናገሩት ከአባታቸው ወይም ከአያታቸው ስም ውስጥ ሁለት ወይም አንድ ፊደል ጎድሎ መመዝገቡ፣ በባንክ ሥራ ላይ ከፍተኛ ጫና እየፈጠረ መሆኑን አቶ ኤፍሬም ገልጸዋል፡፡ 
ከ1,393 በላይ ተመዝጋቢዎች ስም ተጣርቶ ማስተካከያ እንደተደረገ የገለጹት አቶ ኤፍሬም፣ በቀጣይም ሌሎች አቤቱታ የቀረበባቸውን ለማስተካከል በማዕከል ደረጃ እየታየ መሆኑንና ትክክለኛ ሆኖ ከተገኘ የሚስተካከል መሆኑን አስታውቀዋል፡፡ ተመዝግበውና መቆጠቢያ ደብተር ብቻ ይዘው ሳይቆጥቡ ዝም ብለው የከረሙ ካሉ፣ መሥፈርቱን አሟልተው ከተመዘገቡትና በወቅቱ የተወሰነውን መቆጠብ ከጀመሩት ጋር እኩል ስለማይታይ እንዳልተመዘገቡ እንደሚቆጠርም አቶ ኤፍሬም አክለዋል፡፡ 

Saturday, June 14, 2014

ወጣቶቹና- ቅዳሜ፣ አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት

ወጣቶቹና- ቅዳሜ፣ አንዷን ቅዳሜ በፍርድ ቤት

Jailed blog9 bloggers in court

ጽዮን ግርማ
tsiongir@gmail.com
ለአብዛኛው ወጣት አዲስ አበባ ላይ ‹‹ቅዳሜ›› ትርጉም አላት፡፡ የሣምንቱን የሥራ ቀናት በየፈርጁ ያሳለፈው ኹሉም ወጣት ‹‹ቅዳሜ››ን ደግሞ እንደየ ምድቡ ይውልባታል፡፡ እንደሰማኹት ከኾነ ለዞን ዘጠኝ አባላትና ጓደኞቻቸውም ቅዳሜ ልዩ ቀን ናት፡፡ ለወጣቶቹ አብሮነት የጡመራ መድረኩ ቢያግዛቸውም ከዛ በላይ ግን ጓደኝነታቸው ቤተሰባዊነትን ፈጥሮላቸው አብዛኛውን ቅዳሜ እንደየ ቅርበታቸው አብረው ያሳልፋሉ፡፡
አብረው እስረኛ ይጠይቃሉ፣የታመመን ያጽናናሉ፣በጋራ ምሳ ይቋደሳሉ፣የተለየ ዝግጅት ካለም አብረው ይሳተፋሉ፡፡ ከዚህ የተረፈ ጊዜ ካላቸው ደግሞ ፈጣንንና ነጻ የገመድ አልባ ኢንተርኔት አገልግሎት በሚገኝበት ሆቴል ገብተው ዓለም በምን ኹኔታ ላይ እንዳለች ለመከታተል ይሞክራሉ፡፡ አገሪቷ ውስጥ ባለው ከፍተኛ የኢንተርኔት ኮኔክሽን ችግር ምክንያት አብዛኛው ጋዜጠኛና ጥቂት ወጣቶች የእነዚህ ትልልቅ ሆቴሎች ገመድ አልባ ኢንተርኔት ተጠቃሚ ነው፡፡ በቅዳሜ ወደእነዚህ ሆቴሎች ጎራ ያለ ከጦማሪያኑ ወይም ከጋዜጠኛEthiopia bloggers in court አንድ ሰው ሊያገኝ ይችላል፡፡ በቃ ሲገናኙ ሰላም ተባብለው መቀላቀል ነው፡፡እናም በአንድ ጉዳይ ጨዋታ ጀመራል፡፡ አብዛኛው ጨዋታ በአገር ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሊኾን ይችላል፡፡ ኮምፒዩተሮቻቸውን እየነካኩ ስለ አገራቸው ግድ ያላቸውን ይነጋገራሉ፣ይከራከራሉ አሊያም ይጨቃጨቃሉ፡፡መሄጃው ሰዓት የደረሰበት ደግሞ ተሰናብቶ ይሄዳል፡፡በእነዚህ ሆቴሎች በቀጠሮ የሚገናኝ ሰው የለም፡፡‹‹የት ነህ? የት ነሽ?›› የሚለው የስልክ ጥያቄም ለመገናኘት በቂ ነው፡፡
የተስፋዓለም ቅዳሜ ደግሞ ሌላ ነበረች፡፡ሥራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ አብዛኛውን አርቦች ከእነ ለሊታቸው በሥራ ያጠፋቸዋል፡፡ቅዳሜንም ረፈድ አድርጎ ይነሳል፡፡ እናም የመጀመሪያ ሥራው ለሕትመት የበቁ ጋዜጣና መጽሔቶችን አበጥሮ ማንበብ ነው፡፡ በማንበብ ብቻም አያቆምም፤ ከዘገባዎቹ አብዛኖቹ የተሠሩት በጓደኞቹ አሊያም በሚያውቃቸው ጋዜጠኞች ስለሚኾን ስልክ ይደውላል፡፡ ከዘገባዎች ውስጥ ተስፋዓለምን የሚያስደስቱት በጣም ጥቂቶቹ ብቻ ሊኾኑ ስለሚችሉ የስልክ ልውውጦቹ ‹‹እንዲህ ብታደርግ/ብታደርጊ ኖሮ፣እንትናን ብታናግረው በዚህ ጉዳይ ላይ መረጃ ይሰጥህ ነበር፣እዚህ ቦታ እኮ እንዲህ ዓይነት መረጃ ነበር፣ይሄ እኮ ከዚህ በፊት እንዲህ ያለ ሕትመት ላይ ወጥቷል፣እውነቱን ለመናገር ይሄ ለሕትመት የሚበቃ ዘገባ ነው ብዬ አላምንም›› በሚሉ አስተያየቶች የተሞሉJailed Ethiopian bloggers appeared in court ነበሩ፡፡ በዚያው ልክ ደግሞ የሚያስደስተውን ዘገባ ሲያነብ ወይም ፕሮግራም ሲሰማ አዘጋጁን አወቀው አላወቀው ስልክ አፈላልጎ በመደወል ያበረታታል፡፡ የተስፋዓለም ግማሽ ቅዳሜ የምታልቀው ይህን ሲያደርግ ነው፡፡
አኹን እነዚህ ወጣቶች ቅዳሜያቸውን በፌደራል ወንጀል ምርመራ መምሪያ (ማዕከላዊ) ፖሊስ ተነጥቀዋል፡፡ ሃምሳ ቀናት ታስረው ዘጠኝ ቅዳሜን አጥተዋል፡፡ እንዳሻቸው የሚያደርጓትን ቅዳሜ አኹን እነርሱ አያዙባትም፡፡ ከጠዋቱ ዐስራ ሁለት ሰዓት ሲል ከእንቅልፋቸው ይቀሰቀሳሉ፡፡ ለቁርስ ዳቦ በሻይ ይሰጣቸዋል፡፡ (ቤተሰብ የሚያወስድላቸው ምግብ ቁርስ ከበሉ በኋላ ነው የሚደርሳቸው) እናም ተመልሰው ገብተው ይዘጋባቸዋል፡፡አብዛኞቹ ለየብቻ ከሌሎች እስረኛ ጋር የታሰሩ ሲኾን ሁለት፣ ሁለት ተደርገው የታሰሩም አሉ፡፡እናም ከምርመራ የተረፈ ቀናቸውን በዝጉና በጨለምተኛው ክፍል ያሳልፋሉ፡፡ በአንዷ ቅዳሜ ደግሞ እንደዛሬው ፍርድ ቤት ይቀርባሉ፡፡
አንዷን ቅዳሜ- በፍርድ ቤት
ሦስቱ ወጣቶቹ እነርሱ በማያዙባት ቅዳሜ እጆቻቸውን በካቴና ታስረው ፒያሳ በሚገኘው የፌደራል መጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት ግቢ ውስጥ ሲደርሱ ከሌላው ጊዜ የበለጠ ቁጥር ያለው በዐይን ግምት ሦስት መቶ የሚደርስ ችሎት ተከታታይ በግቢ ውስጥ ተገኝቶ ነበር፡፡ የዛሬዎቹ ጠባቂ የፌደራል ፖሊሶች ባለፈው ጊዜ ከነበሩት ሻል ያሉ ስለነበሩ ቤተሰቦች ችሎት ውስጥ ገብተው እንዲታደሙ ባይፈቀድላቸውም ግቢ ውስጥ ከመቆም የከለከላቸው ወይም ያመናጨቃቸው አልነበረም፡፡ bloggers in court Addis Ababa, Ethiopia
ከጠዋቱ አራት ሰዓት ከሃያ ደቂቃ አካባቢ ሲኾን ችሎቱ በሴት ዳኛ በመሰየሙ፤ጋዜጠኛ ኤዶም ካሳዬ፣የዞን ዘጠኝ ጦማሪዎቹ ናትናኤል ፈለቀና አጥናፉ ብርሃነ እጃቸውን በሰንሰለት እንደታሰሩ ወደ ግቢው ገቡ፡፡ ዛሬ ወጣቶቹ በስስ ፈገግታ ‹‹አይዞአችሁ ደህና ነን›› የሚል የተስፋ ምልክት ለቤሰተቦቻቸውና ለጓደኞቻቸው አሳይተዋል፡፡ ከእነርሱ ቀጥለው በፖሊስ ታጅበው የገቡት ጋዜጠኛ ተስፋዓለም ወልደየስ፣ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስና የሕግ መምሕርና የዞን ዘጠኝ ጦማሪ ዘለዓለም ክብረት እጆቻቸው በካቴና እንደታሰረ ለቤተሰቦቻው ሰላምታን ሰጥተዋል፡፡ የእነርሱ ፈገግተኛ መኾን ለቤተሰቦቻቸው፣ለጓደኞቻቸውና ለወዳጆቻቸው ጥቂትም ቢኾን እፎይታን ሰጥቷል፡፡
ተጠርጣሪዎቹ ችሎት የቀረቡት እንደወትሮው ኹሉ በሁለት መዝገብ ተከፍለው ቢኾንም ፖሊስ ያቀረበው ምክንያትና መከራከሪያ አንድ ዓይነት ነበር፡፡ ችሎቱ ከተሰየመ በኋላ ፖሊስ በተሰጠው ጊዜ ቀጠሮ በርካታ ጉዳዮችን ሲመረምር መቆየቱንና አሁንም ያልተጠናቀቀ ምርመራ ስለሚቀረው ተጨማሪ ሃያ ስምንት ቀናት እንዲሰጠው ጠይቋል፡፡
ጠበቃው አቶ አመሐ፤‹‹ፖሊስ ከዚህ ቀደም በወሰደው ጊዜ ቀጠሮ ሰንድ ለማስተርጎም፣ የምስክሮችን ቃል ለመቀበል፣ኢሜሎቻቸውን ለመፈተሽ እንዲሁም ያልተያዙEthiopian Jailed bloggers ግብረአበሮቻቸውን ለመያዝ ብሎ እንደነበርና አሁን ዝም ብሎ በጥቅሉ በርካታ ሥራዎችን ሠርቼያለሁ እንደገና ይጨመርልኝ ማለቱ አግባብ አይደለም›› ሲሉ አመልክተው ነበር፡፡ ዳኛው ፖሊስ የሠራውን ሥራና የሚቀረውን ምርምራ እንዲያስረዳ በማዘዛቸው፣‹‹ከሠራናቸው በርካታ የምርመራ ሥራዎች መካከል የተባባሪዎቻቸውን ቤት ፈትሸናል፣ለተለያዩ ባንኮች የተጠርጣሪዎቹን ዝርዝር መረጃ እንዲሰጡን ጠይቀን ከተወሰኑት ምላሽ አግኝተናል፣የተወሱ ምስክሮችንን ቃል ተቀብለናል፣ ከትርጉም ሥራውም የተወሰነውን ሠርተናል፡፡ ግብረአበሮቻቸው ወደ ክፍለ ሃገርና ወደ ተለያዩ አገራት እየሸሹ መያዝ ስለተቸገርን የፖሊስ ኃይል አሰማርተን እያፈለግናቸው ነው እነርሱንም መያዝ ይቀረናል፡፡›› በማለት ተናግሯል፡፡
አቶ አመሐ በበኩላቸው፤‹‹ፖሊስ ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ስር ካዋለ ሃምሳ ቀናት ሞልቶታል፡፡ እነዚህ የሚላቸውን ነገሮች አጠናቆ ለመጨረስ የነበረው ጊዜ ከበቂ በላይ ነው፡፡አሁንም ቢኾን እነዚህን ምርመራዎች ለማድረግ የደንበኞቼን አስሮ ማስቀመጥ አስፈላጊ አይደለም ስለዚህም ፍርድ ቤቱ የዋስትና መብቻውን ሊያከብርላቸው ይገባል፡፡ ይህን ጥያቄ ፍርድ ቤቱ ባይቀበለው እንኳን ከዚህ በኋላ ፖሊስ በሚሰጠው ሃያ ስምንት ቀናት ጊዜ ውስጥ ምርመራውን አጠናቆ እንዲመጣ፤አጠናቆ ባይመጣ ደግሞ ጥያቄው ተቀባይነት እንደማይኖረው ተደርጎ ይመዝገብልን›› በማለት ጠይቀዋል፡፡
ዳኛዋ አቤቱታውን ካደመጡ በኋላ፤ፖሊስ ከዚህ በኋላ ሲቀርብ ለተጨማሪ የምርመራ ቀነ ቀጠሮ መጠየቂያ አሁን የጠቀሳቸውን ምክንያቶች በምክንያትነት ይዞ እንዳይቀርብ በማሳሰብ የጠየቀውን የሃያ ስምንት ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ ቀጠሮ ፈቅደዋል፡፡zone9 bloggers in court
በዛሬው ዕለት ችሎት ከቀረቡት መካከል ጋዜጠኛ አስማማው ኃይለ ጊዮርጊስ ፤ከፍተኛ የኾነ የጀርባ ሕመም ስላለበት ወንበር እንዲገባለት መጠየቁንና እስካኹን ሊገባለት እንዳልቻለ ጠቅሶ ፍርድ ቤቱ ትእዛዝ እንዲሰጥለት አመልክቷል፡፡ ዳኛዋ ከምንም ነገር በላይ የጤና ጉዳይ ቅድሚያ ሊሰጠው እንደሚገባ በማሳሰብ የጠየቀው ወንበር እንዲገባለት ሲሉ ተናግረዋል፡፡ በችሎት የተገኘው መርማሪ ፖሊስ፤‹‹በአጋጣሚ የእርሱ መርማሪ እኔ ነኝ የጀርባ ሕመም እንዳለበት ነግሮኛል፡፡ ወንበር እንዲገባለት ግን አልጠየቀኝም፡፡ አሁን ቢኾን ይህ በጣም ቀላልና እዛው እኛው ጋር ሊያልቅ የሚችል ነገር ነው፡፡ ችግር የለም እናስገባለታለን›› ሲሉ ቃላቸውን ሰጥተዋል፡፡
እስረኞቹ ከችሎት ሲወጡ እንደ አገባባቸው በፈገግታ ሰላምታ እየሰጡ ሲኾን ችሎቱን ለመከታተል መጥቶ ፍርድ ቤቱ ግቢ ውስጥ ቆመው ሰውም እጁን በማውለብለብ ተሰናብቷቸዋል፡፡ (ፎቶ አዲስ ስታንዳርድ)