Sunday, January 19, 2014

በህይወት የሚገኙ አካለ ሰንኩላን እህቶቻችን እና ባለቤት አልባው የዜጎቻችን አስከሬን ብሶት በሳውዲ አረቢያ ሆስፒታሎች ።


ላለፉት ተከታታይ ፫ ሳምንታት በርካት ኢትዮጵያውያን ከ ሳውዲ አረብያ ጂዛን፡ወደ አዲስ አበባ በቀጥታ በረራ እየተሸኙ ሲሆን በመኪና አደጋ እና መሰል ተዛማጅ አደጋዎች ቆመው መራመድ የማይችሉ ወገኖቻችን በሳውዲ አየርላይንስ እንደማይጫኑ በመግለጹ ለከፍተኛ የሞራል ዝቅጠት መዳረጋቸውን ምንጮች ይገልጻሉ።በተለይ በጂዛን ከተማ በአቡሰዳድ ኣድ ደርብ ሆስፒታል ለ፫ አመታት ያልጋ ቁራኛ እንደሆነች የሚነገርላት ወጣት ከዲጃ መሓመድ ሑሴንን አብነት የሚጠቅሱት እነዚህ ምንጮች ።



ዛሬ በመልካም ጤንነት ላይ የሚገኝ ኢትዮጵያውያን ለሃገራቸው በመብቃት ሰቃይ እና በደል ሲፈራረቅባት የኖረውን ህይወታቸውን ከሞት መታደግ ሲችሉ በተመሳሳይ ሞት ቀድሞት በለስ የቀናው የወገን ሬሳ በሳጥን ታሽጓ ለህገሩ አፈር ሲበቃ እንደነ ከድጃ ያሉ ዜጎች በሳውዲ አረቢያ ሆስፒታሎች የሚደርስላቸው አጠተው ሞታቸውን ሲጠብቁ ማየት ምንኝኛ እንጀት እንደሚበላ ይናገራሉ ። በአካላቸው ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷባቸው የአልጋ ቁራኛ ከሆኑ ወገኖቻችን መሃከል አንዶ የሆነችው ወጣት ከድጃ መሃመድ ከኢትዮጵያ ከቆንስላ ፅ\ቤት ተወካዮች የተሰጣት ምላሽ ተስፋ አስቋራጭ፡መሆኑን የሚገልጹ ወገኖች የወጣቷ ህይወት ቆንስላው በኢትዮጵያ አየር መንገድ እንጂ በሳውዲ አየር መንገድ ማሳፈር እንደማትችል ከማስረዳት ባሻገር እስካሁን የረባ ነገር ማድረግ እንዳልቻለ ገልጸዋል ።

ለዚህም በጂዛን የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ሊቀመንበር አቶ ግደይ ግራማ ማምሻውን ከጂዛን ፡ ጀዳ ፡አዲስ አበባ ትራንዚት ቲኬት ቆርጣ ወጣቷ መሄድ እንዳለባት እንደተናገሩ የሚገልጹት ምንጮች ። ወጣቷ በደረሰባት የመ ኪና አደጋ ቀሪ ሰውነትዋን ማዘዝ እንደማትችል እና « ከሽንጥዋ በታች » በድን ከመሆኖ ባሻገር ያለ «ዳያፐርና ካታተር » የ ሽንት ማስወገጃ ቱቦ ስለማትንቀሳቀስ እርዳታ እና የቀርብ ክትትል እንደሚያሻት እያወቁ አንጻራዊ እርዳት ከማድረግ ይልቅ ከጂዛን ጅዳ የምሄዱን ሃላፊነት በዝች ባልታደለች ወጣት ላይ መጣላቸው ሰባዊ ነት የጎደለው መሆኑንን ይናገራሉ ።

Ethiopian Hagere's photo.ለደረሰባት የመኪና አደጋ የኢንሹራንስ መብቷን የሚያስከብርላት እጥታ ከወግቧ በታች በድን ሆና ሃገር ለመግባት መገደዷን የሚናገሩ የአካባቢው ምንጮች ለዚች አካለ ሰንኩል ወጣት ፧የጉዞ ሰነድዋን የሚያዘጋጅላት ፧ከጂዛን እስከ ጀዳ የስምንት መቶ ኪሎ መትር ርቀት ከዛም ጅዳ ስትደርስ ተቀብሎ የሚያስተናግዳት ወገን እንደሌላት የሚናገሩ እንዚህ ወገኖች በዚህ ዙሪያ ወገናዊ ትብበር እንዲያደርጉ ጉዳዩ ለሚመላከታቸው አካላት በጅዳ ጄነራል ዘነበ ከበደ ለሚመራው የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት አመልከተው መፍትሄ እንዳለገኙ የሚገልጹ እነዚህ ምንጮች በተመሳሳይ መልኩ ወደ ሃገር መግባት እየፈለጉ መግባት ያልቻሉ በየቤቱ እና በየሆስፒታሉ የሚገኙ አካለሰንኩል ዜጎቻችን ያለረዳት ወገን አልባ ሆነው ለከፋ ስቃይ እና በደል እየተዳረጉ መሆኑገልጸዋል።

ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ድረስ ወጣቷ ያለጠያቂ እና ደጋፊ ሆስፒታል ውስጥ፡መሆኗን ለማረጋጋጥ፡ተችሎል ። በተመሳሳይ ሁኔታ በከባድ የመኪና አደጋ ማየት እንጂ መስማትም ሆነ መናገር አሊያም መንቀሳቀስ የማይችለው ኢትዮጵያዊ ወጣት በዛው ሆስፒታል ውስጥ እንደሚኖር እንዚሁ ምንጮች ገልጸዋል። በሳውዲ አረቢያ የተለያዩ ሆስፒታሎች ከሚገኙ አካለ ሰንኩል ወገኖቻችን ባሻገር ሪያድ ጅዳ ጂዛን መዲና ወዘተ በሚገኙ ሆስፒታሎች ውስጥ አድራሻቸው የማይታወቅ በተለያዩ አደጋዎች ህይወታቸው ያለፈ በሺህ የሚቆጠር የኢትዮጵያውያን ሬሳ እንደሚገኝ ይታወቃል።

Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ
L 

No comments:

Post a Comment