በርሱፈቃድ በጋሻው ተሾመ የተባለው የ24 አመት ወጣት ቦሌ ሚሊኒየም አዳራሽ አካባቢ በሚገኘው የህብረት ባንክ በጥበቃ ሰራተኝነት ለአንድ ወር ሲሰራ የቆየ ሲሆን ዛሬ 6 ሰዓት አካባቢ ባንኩ ለጥበቃ በሰጠው ጠመንጃ ሶስት ግዜ በመተኮስ ነው ራሱን ያጠፋው፡፡
በአካባቢው የነበሩ የአይን እማኞች ሟቹ ሁለት ግዜ በአገጩ ስር ተኩሶ ራሱን ከሳተ በኋላ በሶስተኛው ጥይት ጭንቅላቱን መትቶ ራሱን ሲያጠፋ ማየታቸውን ተናግረዋል፡፡

የሟች ባልደረቦች እንደሚሉት ከሆነ ሟች በጠዋት ወደስራ ሲመጣ አይኑ ቀልቶ እና የተረበሸ ይመስል እንደነበር እንዲሁም ‹‹በተደጋጋሚም ክርስቶስ አይወደኝም ›› ሲል እንደተሰማ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ ድሬ ትዩብ
No comments:
Post a Comment