Monday, February 24, 2014

የኩዬት መንግስት ኢትዮጵያውያን ሰራተኞች ወደ ሃገሩ ገብተው እንዳይሰሩ እገዳ ጣለ፡፡


የኩዬት የሃገር ውስጥ ጉዳይ ሚንስቴር ኢትዮጵያውያን ወንድ እና ሴት የቤት እና የጉልበት ሰራተኞች ወደሃገሩ ገብተው እንዳይሰሩ ማገዱን አስታውቋል፡፡

የፓስፖርት እና የብሄራዊ ጉዳዮች ምክትል ሃላፊ ሜጀር ጀነራል ፈይሰል አል ናዋፍ እንዳሉት ለኢትዮጵያውያኑ ቪዛ መስጠት የታገደው በኢትዮጵያውያን ሰራተኞች እየተፈጸመ ያለው የግድያ ፣ የስርቆት ፣ የድብደባ እንዲሁም በተለያዩ ጉዳዮች በማስፈራራት ገንዘብ የመጠየቅ ወንጀሎች በመበራከታቸው ነው፡፡

እገዳው ተግባራዊ የሚሆነው ከየካቲት 12 ቀን 2006 ዓ.ም ጀምሮ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

No comments:

Post a Comment