በሪያድ አለም አቀፈ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት የወላጆች ኮሚቴ ዛሬ አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ መለዕክት አስተላለፈ !
በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ተማሪዎች የወላጅ ኮሚቴ እና በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች መሃከል የተፈጠረው እሰጣገባ ከ ሴፕቴምበር 22 2013 በሃላ አደገኛ ሁኔታ ላይ መድረሱን ተከትሎ ኮሚቲው አስቸኳይ ጠቅላላ የወላጆች ስብሰባ ለመጥራት መገደዱን ገልጾል። በተለይ ሴፕቴምበር 24 2013 ዲፕሎማቱ 11 አባልት ያለውን አንጋፍ የወላጅ ኮሚቴ አስጠርተው ለማስፈራራት ያደረጉት ሙከራ ህጋዊ መስረት የሌለው እና አንድ ሉአላዊ መንግስትን እወክላለሁ ኪሚል አካል የሚጠበቅ ባለመሆኑ ዲፕሎማቱ መንግስታችን ከሚያራምደው ልማታዊ አስተሳሰብ እና አቋም አፈንግጠው በመሄድ እያካሄዱብን ላለው ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሳንበገር የልጆቻችን መማሪያ የሆነውን ት/ቤት ከዘራፊዎች ለማስጣል ትግላችንን ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ አጠናክረን እንቀጥላለን ብለዋል። በዚህም መስረት ዛሬ ቀን ሃሙስ ሴፕቴምበር 26 2013 በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከምሽቱ 02 30 ጀምሮ ልዩ ስሙ በተለምዶ አዚዚያ እየተባለ በሚጠራ አካባቢ በሚገኝ የመዝናኛ አዳራሽ፡ውስጥ ስብሰባው እንደሚካሄድ ተገልጾል ።
በመጨረሻ ዘግይቶ የደረሰ ዜና
ይህን ተከትሎ ዲፕሎማቱ በወላጆች የተነሳባቸውን ተቃውሞ ለምታት ህዝቡን በብሄር መከፋፈል ያመቻቸው ዘንድ ዲፕሎማቱ በስራቸው የሚገኙትን የልማት ማህበራት ስራ አመራር አባላት እና አንዳንድ የሃገር ሽማግሌዎች ዛሬ ማታ በኢትዮጵያ ኮምኒቲ አዳራሽ ስብሰባ መጥራታቸውን ለማረጋገጥ ተችሏል።
ሙሉ ዘገባውን ዛሬ ከስብሰባው በሃላ ይጠብቁ
Ethiopian Hagere ሳውዲ አረቢያ «ጅዳ በዋዲ
No comments:
Post a Comment