በዲፕሎማቱ ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሳይሸበር የትምህርት እድል የተነፈጋቸውን ህጻናት ከማሃይምነት ለመታደግ በአቋሙ እንደሚጸና በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት የወላጆች ኮሚቴ ገለፀ።
ትላንት ሃሙስ ሴፕቴምበር 26 2013 ኮሚቲው ለወላጆቹ ባስተላለፈው አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ ማስተላለፉን ተከትሎ ብዛት ያላቸው ወላጆች መገኘታቸውን የሚገልጹት ምንጮች ዲፕሎማቱ የመንግስትን ስልጣን ተጠቅመው በወላጅ ኮሚቴው ላይ ተጸኖ ለማሳረፍ የኮሚቴውን አባላት እምባሲ ድረስ በስልክ አስጠርተው የፈጸሙት ተራ ማሰፈራሪያ እና ዛቻ ህጋዊ መስረት የሌለው እና መንግስት የቆመለትን ልማታዊ አስተሳሰብ በቅጡ ያላገናዘበ መሆኑን በመግለጽ፡ ዲፕሎማቱ የት/ቤቱን የመማር ማስተማር ስረአት ለማደናቀፍ እየፈጸሙ ያለውን ጣልቃ ገብነት ፀረ ህዝብ እና ጸረ ልማት ድርጊት እስከ መጨረሻው እንደሚታገሉ የወላጆቹ ኮሚቴ ደግመው አረጋግጠዋል ።
ወላጆቹ በኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ ስብሰባ ማድረግ እንድሚችሉ በዲያስፖራው ሃላፊ አቶ ተመስገን ኡመር ቀደም ተብሎ በተገባላቸው ቃል መስረት ሴፕቴምበር 22 2013 ምሽት አጠቃላይ የወላጆች ስብሰባ ተጠርቶ እንደነበር በማስታወስ በተጠቀሰው ቀን ብዛት ያላቸው ወላጆች ወደ መሰብሰቢያ አዳራሹ ሲጎርፉ በኤምባሲው ተዕዛዝ በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ በር መዘጋቱ ዲፕሎማቱ ለህዝብ ያላቸውን ንቀት እና የለየ ጠብጫሪ ተግባራቸውን በግልጽ ያሳዩበት አጋጣሚ በመሆኑ የኛ ቅሬታ እና ተቃውሞ በሪያድ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ውስጥ፡ መሽገው ዲያስፖራወን እና መንግስትን ለማራራቅ በኮሚኒቲው አካባቢ ሰላም እያሳጡን ካሉት ዲፕሎማቶች ጋር ነው ብለዋል። ይህ በዚህ እንዳለ በየአቅጣጫው የፈነዳባቸውን ተቃውሞ ማዳፈን የተሳናቸው በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች ወላጆችን በብሄር ከፋፍሎ ለማጋጨት የሚያስችላቸውን እቀድ ማውጣታቸውን የሚናገሩ ውስጥ አዋቂ ምንጮች ዲፕሎማቱ ለዚህ እቅዳቸው መሳካት ያልታወቀ ህገወጥ ቡድን በስውር ሪያድ ከተማ ላይ ማሰማራታቸውን የኢንቨስትመንት እና ቱሪዝም ተጠሪ የሆኑት ዲፕሎማት አቶ ዘላለም የወላጅ ኮሚቲውን ለማስፈራራት ሲናገሩ ከነብረው ገለጻ መረዳት መቻሉን አረጋግጠዋል።
ይህ በዚህ እንዳለ መንግስት ቀደም ብሎ በብሄር ያደራጃቸውን የልማት ማህበራት ዲፕሎማቱ በተጓዳኝነት ለድብቅ አጀንዳዎቻቸው ማስፈጸሚያ ግበአት ለማድረግ የማህበራቱን ስራ አመራር አባላት ትላንት ሃሙስ ሴፕቴምበር 26 ቀን 2013 ምሽት በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒት አዳራሽ፡ ጠርተው በሚስጥር እንዳነጋገሯቸው የሚጠቅሱት የአይን እማኞች አባላቱ በአካቢያቸው የሚገኙትን የልማት ማህበራት አባላት እና ደጋፊዎች የፊታችን አርብ ኦክቶበር 4 2013 ኤንባሲው በጠራው የወላጆች አጠቃላይ ስብሰባ ላይ እንዲገኙ እና የወላጅ ኮሚቴው ከተወሰኑ ነፍጠኛ እና ጽንፈኛ የአማራ የኦሮሞ እና የስልጤ ብሄረሰቦች የተውጣጡ ግለሰቦች መሆናቸውን በማስረዳት ቅስቀሳ ማድረግ እንደሚገባቸው መመሪያ ቢሰጡም በአብዛኛው አመራር አባላት ዘንድ ተቀባይነትን ማጣቱን ገልጸዋል።
አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ከ20 አመት በፊት ሻይ እን ዳቦ ሸጠው ያቋቋሙት ህጋዊ ንብረታቸው መሆኑንን በመረጃ እስደግፈው የሚናገሩት ወላጆች በየትኛውም አቅጣጫ ዲፕሎማቱ እየፈጸሙ ባለው ከፋፋይ ሴራ ሳንጠለፍ በቡድን እና በግል ለሚሰነዝሩብን ማስፈራሪያ እና ዛቻ ሳንበረግግ ህጋዊ እና ሰላማዊ በሆነ መንገድ ዲፕሎማቱን ለህግ እናቀርባቸዋለን ብለዋል።
በተለይ ላለፉት 5 አመታት ምንም አይነት ኦዲት ተደርጎበት የማያውቀው ት/ቤት ካዝና ላይ ብቅርቡ በተደረገው ማጣራት እስከ ከ1.5 ሚልዮን ሪያል ወይም በአሁኑ የሃገራችን ምንዛሪ «ከ5ሚሊዮን 8መቶ ሺህ ብር» በላይ ጉድለት ማሳየቱን የሚናገሩ እነዚህ ምንጮች ዲፕሎማቱ ከተማሪዎቹ ወላጆች ጋር እንካሰላምታ ውስጥ፡እንዲገቡ ያሰገደዳቸው አንዱ ምክንያት ይህ ሊሆን እንደሚችል ይገምታሉ። ዲፕሎማቱ በት/ቤቱ የውስጥ ጉዳይ ከ3 አመት በፊት እጃቸውን በቀጥታ በማስገባት ከወላጆች እና ከኮሚኒቲው ፍላጎት ውጭ፡ በእጅ አዙር ኮሚኒቲው ት/ቤት ካዝና ውስጥ እጃቸውን ሲዶሉ እንደ ነብር የሚታወቅ ሲሆን ከቀር ግዜ ውዲህ በዲፕሎማቱ እና በአጠቃላይ የሪያድ መህበረሰብ መሃከል በተፈጠረው አለመግባባት ግዜያችንን ሳንጨርስ መንግስት ወደ ሃገር ካስጠራን ገበናችን አደባባይ እርቃኑንን ይቀራል በሚል ስጋት የተጠቀሰውን ት/ቤት እስከ ናካቴው ለማዘጋት አሊያም ለኢንቨተር ለመሸጥ እቅድ እንደነበ ራቸው ለመረዳት ተችሎል።
የወላጆ ኮሚቴው ቀደም ስል ካቀረባቸው 4 ጥያቄዎች የት/ቤቱን ንብረት ከዘራፊዎች ለመከላከል ት/ቤቱን ወደ ቀድሞ ስሙ «በሪያድ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት» እንዲለወጥ ማስቻል ግንባር ቀደም የትግላቸው መነሻ እንደሆነ በመግለጽ ዲፕሎማቱ ወላጆች ላቀረቦቸውን ህጋዊ ጥያቄ ተገዢ ሆነው በአግባቡ መመልስ ተስኖቸው ሰላማዊ ወላጆችን በጅምላ በሸባሪነት በመፈርጅ የዲያስፖራውን ጥያቄ የትኩርተ አቅጣጫ ለማስለወጥ፡እያደረጉ ያለው ጥረት አምኖ የወከላቸውን መንግስት እና በሪያድ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ ማህበረሰብ ክቡር የሚነካ ወራዳ ተግባር መሆኑን ገልጸዋል። በዚህ መሰረት መንግስት ውጭ ሃገራት የተሰማሩ ዲፕሎማቶች በህግ አግባብ መጠየቅ የሚቻልበት እድል ካለ የፌደራሉ ስነ ምግባር እና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ድንበር ተሻግሮ በሪያድ የኢትዮጵያ አለመ አቀፍ ት/ቤት ካዝና ላይ የተፈጸመውን አስነዋሪ ተግባር በመመርመር በሪያድ የኢትዮጵያውያ ኤንባሲ ህንጻ ውስጥ፡የመሸጉትን ስረአት አለበኛ ዲፕሎማቶች እና ከት/ቤቱ ካዝና ጋር ግንኙነት ባላቸው ተባባሪ ወገኖች ላይ መረጃ በማጠናቀር አስፈላጊውን ህጋዊ እርምጃ ማስወሰድ ፡እንደሚጠበቅበት አበክረው አሳስበዋል።
እንደሚታወቀው በሪያድ የኢትዮጵያ ዲፕሎማቶች በኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚንስቴር መ/ቤት የሴቶች እና የህጻናት ጉዳይ ተጠሪ ክብርት ወ/ሮ ደስታ ወ/የሃንስ በተገኙበት ስብሰባ በሪያድ ኢትዮጵያዊው ዲያስፖራ በዲፕሎማቱ ላይ ያሰማውን ተቃውሞ እና ቅሬታ ተከትሎ በሪያድ የኢትዮጵያው አምባሳደር መሃመድ ሃሰን በስቸኳይ ወደ ኢትዮጵያ መጠራታቸው ይታወሳል።
Ethiopian Hagere ከሳውዲ አረቢያ «፡ጅዳ በዋዲ»
No comments:
Post a Comment