Saturday, March 15, 2014

በጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ላይ የተከፈተውን ስም ማጥፋት ዘመቻ በሳውዲ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ተቃወሙ « ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እረፍት ላይ ነው »


ሰሞኑንን የታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ከድህረ ገጽ መራቅን ተከትሎ በተለዩዩ የፌስ ቡክ ገጾች የሚነገሩ መላምቶች ከእውነት የራቁ እና ፍጹም የታላቁን ጋዜጠኛ ባህሪ የማይወክሉ በኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ላይ የተሰነዘረ ተራ ስም ማጥፋት ዘመቻ መሆኑንን በሪያድ እና ጅዳ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ገለጹ ። ደከመኝ ሰልቸኝ ሳይል የማለዳ ወግ በሚል ር ዕስ በአረብ አለም የሚገኙ ወገኖቹን እሮሮ በማሰማት የህዝብን ፍቀር እና ክብረን ያገኘው ታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ከማርች 4 2014 ጀምሮ እረፈት ላይ መሆኑን የሚናገሩ ምንጮች ይህን አጋጣሚ ተጠቅመው አንዳንድ ግለሰቦች በግል ጥላቻ በዚህ ታላቅ ጋዜጠኛ ላይ እይናፈሱ ባለው ወሬ ህዝቡ እንዳይደናገር አክለው ገልጸዋል። 

ታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በቤት ሰራተኝነት ወደ ሳውዲ አረቢያ በሚመጡ እህቶቻችን ላይ የሚፈጸመው መረን የለቀቀ ግፍ እና በደል እንዲቆም እያሰተላለፈ ባለው የማለዳ መልዕክቱ ይህ ታላቅ ጋዜጠኛ በወገኖቻችን ህይወት በሚነገዱ ጥቂትለሰቦች በአይነ ቁራኛ እንደሚጠበቅ ይታወቃል ። በተለይ ከኢትዮጵያ በኮንተራት ወደ ሳውዲ የመጡ እህቶቻችንን በሃይል ለባእዳን አሳልፈው በመስጠት በወሲብ ንግድ ላይ በማሰማራት በወገኖቻችን ስበዕና ላይ ግፍ ሲፈጽሙ እና ሲያስፈጽሙ የነብሩ ግለሰቦች ለ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ የተለያዩ ሰሞችን በመስጠት ከህዝበ ሙስሊሙ ወግናችን ጋር ለማጋጨት ያልፈነቀሉት ድንጋይ ያልበጠሱት ቀጠል የለም። በሳውዲ አረቢያ በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ዘንድ በስው አክባሪ ነቱ እና በኢትዮጵያዊ ጨዋነቱ የሚታወቀው ይህ ታላቅ ጋዜጠኛ በመካከለኛው ምስራቅ በተለይ ጅዳ እና ሪያድ ከተማ ውስጥ በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመውን ስቃይ እና በደል ለህዝብ በአደባባይ ከመግለጽ እንዲቆጠብ በተጠቀሱት ጋጥወጦች በድምጽ እና በጽሁፍ መሳፈራሪያዎች ቢደርሱትም ቅንጣጥ ያህል ሳይሸበር ሳይማር ላስተማረው ህዝብ መስወአት ለመሆን የህዝብን እሮሮ በማሰማት አንገቱን ለስይፍ ግንባሩን ለጥየት የሰጠ ያልተነገረለት ጀግና መሆኑን ከልጅ አስከ አዋቂ ለሃገር እና ለወገን ተቆርቋሪ የሆነ ሁሉ ይመስክርለታል።፡፤ 

ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እየፈጸመ ላለው ታልቅ ተግባር ክብር እና ምስጋና ይገበዋል የሚሉ በጅዳ እና በሪያድ የሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ስደተኞች እንደነዚህ አይነቶችን ይህዝብ ልጆች ለማበረታት የክበር ሽልማቶች መዘጋጀት እንዳለባቸውም አመልክተዋል። ከእንግዲህ በአረቡ አለም በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው ስቃይ እና በደል ማብቂያ ሊበጅለት የሚሉ የአንድ በዕድሜ ባለጸጋ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ አባት ሳውዲ አረቢያ የተቀደሰችዋ መካ ከተማ ውስጥ ላለፉት 40 አመታት መኖራቸውን ገልጸው በወገኖቻችን ላይ የሚፈጸመው ስቃይ እና በድለ ቀደም ብሎ ይሰማ እንዳልነበር አስታውሰው ዛሬ በጀርመን ድምጽ አማርኛ ፕሮግራም እና በተለያዩ ድህረ ገጾች መነበቡ «አልህምዱሊላሂ» ፈጣሪን ሊመሰገን ይገበዋል በለው ይህን ሁሉ ላደረገው ለታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ እና መስል ወገኖቻችን እድሜን እና ጤናን እንደሚመኙ አክለው ገልጸዋል። ይህን ተከትሎ በአንዳንድ ወሮ በሎች በጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ላይ በግልጥላቻ ሰሞኑንን ሰለሚናፍሰው ወሬ የተለመደ እና ቦታ እንደማይሰጡት ገልጸው በፌስ ቡክ ገጽ ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞችን ስም የሚያጠፉት ወገኖች በእህቶቻችን ላይ በድል እና ግፍ ሲፈጸም የከረሙ ሴጣኖች በመሆናቸው እነዚህ ግለሰቦች የኢትዮጵያን ሙስሊሙም ሆነ ክርስቲያኑን ማህበረሰብ ስለማይወክሉ ከወዲሁ ሊወገዙ እንደሚገባቸው ተናግረዋል ። 

 ሰሞኑንን ታላቁን ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ከድህረ ገጽ መጥፋን ተከትሎ አንዳንድ ግለስቦች በተለያዩ የእስልምና ሃይማኖት ተከታይ ወገኖቻችን ስም በከፈቱት የፌስ ቡክ ገጽ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በሳውዲ አረቢያ ህግ የተከለክሉ ነገሮችን ፈጽሞ የታሰረ አስመስለው ውዠንበር በመንዛት ላይ ይገኛሉ። በመሆኑም የነዚህ ግለሰቦች ተዕለኳ ምን እንደሆነ ለግዜው ግልጽ ባይሆንም ታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ በአሁኑ ግዜ እረፍት ላይ መሆኑንን በመረዳት ህዝብ በተለያዩ አቅጣጫዎች በሚነዙ በሬ ወለደ ውዠንብሮች እንዳይደናገጥ ውስጥ አውቂ ምንጮች ገልጸዋል ። 

Ethiopian Hagere ጅዳ በዋዲ     ( እረፍት ላይ የሚገኘው አንገቱን ለሰይፍ ግንባሩን ለጥየት የሰጠ ታላቁ ጋዜጠኛ ነብዩ ሲራክ ) ።

No comments:

Post a Comment